የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) ገለፁ።

የለውጡ መንግስት ለከተሞች እኩል የመልማት ዕድልን አስገኝቷል-የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች

በዲላ ከተማ "የመጋቢት ፍሬዎች ለኢትዮጵያ ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል የለውጡን መንግሥት የሚደግፍ ህዝባዊ ሰልፍ ተካሂዷል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በዚህ ጊዜ እንዳሉት በለውጡ አመታት በክልሉ ከፍተኛ የልማት እድገት ተመዝግቧል።

ለዚህም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ትግበራና ለሰው ተኮር እድገት የተሰጠው ትኩረት የራሱ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰዋል።

በከተሞች ኮሪደር ልማትን ጨምሮ የመሠረተ ልማት ማስፋፊያ እንዲሁም በገጠር በግብርና እና በማዕድን ዘርፎች እምርታ መታየቱን ለአብነት አንስተዋል።

እነዚህን የለውጥ ጉዟችንን ስነዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶችን በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉም ገልፀዋል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዞኑ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት አርሶ አደሩ በአመት ሶስት ጊዜ እንዲያመርት በማድረግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ገበያ ተኮር ምርት በስፋት መመረቱን ጠቅሰዋል።


የብዝሃ ኢኮኖሚ ዘርፍ ትግበራ ግብርናውን በማዘን ከዞኑ በአማካይ ከ40 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ከማቅረብ ባለፈ በሌሎች ዘርፎችም የገቢ አቅም ማሳደግ መቻሉን አንስተዋል።

የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማጠናከርም የብልጽግናን ጉዞ ለማስቀጠል እየተሠራ መሆኑንም ገልፀዋል።

ከተሞችን የለውጥ ማዕከል የማድረግ ሀገራዊ ጥረት በዲላ ከተማ በተጨባጭ እየታየ ነው ያሉት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ናቸው።


ይህም የለውጡ መንግሥት ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እና ፖለቲካዊ ተሳትፎን ያረጋገጠ መሆኑን ነው ያነሱት።

ባለፉት የለውጥ አመታት ብቻ የከተማውን ነዋሪ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ከ 252 በላይ የልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን ተናግረዋል፡፡

እነዚህ የለውጥ ትሩፋቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የነዋሪው የነቃ ተሳትፎ እንዲጠናከርም ጥሪ አቅርበዋል።


ከድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል መምህርት ስመኝ ታደሰ በሰጡት አስተያየት የለውጥ ዓመታትን መዘከር ተጨባጭ እድገትን ማስቀጠል ነው ብለዋል።

የለውጡ መንግሥት ሀገር በችግር ውስጥ በነበረችበት ወቅት ወደ ስልጣን በመምጣት ኢትዮጵያን ያሻገረ መሆኑን ጠቅሰው አጋርነታቸውን ለማረጋገጥ በድጋፍ ሰልፉ መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026