የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን በመጠበቅ ለቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልፅግና ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ዋና አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ ገለጹ።

የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ''የቀይ ባሕር እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ቀጣና የባሕር አስተዳደር፤ አካታችነትና ትስስር ለጋራ ጥቅም'' በሚል መሪ ሃሳብ አራተኛውን ዓመታዊ የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።


የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ዋና አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ሉዓላዊ መዳረሻ ጥያቄ ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ስትራቴጂክ መሰረትና ቅቡልነት ያለው ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከባሕር በር መዳረሻዎቿ የተገለለችበት ኢ- ፍትሕዊ በደልም በቀጣናዊ ጂኦ - ፖለቲካዊ የኃይል ሚዛንና የባሕር ላይ ደኅንነት ጥበቃ የሚጠበቅባትን ገንቢ ሚና እንደገደበው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገትና የህዝብ ቁጥር የልማት ፍላጎት ለማሳለጥም አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ጠንካራ የባሕር ኃይል ግንባታም የባሕር ላይ ውንብድና፣ ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር፣ሽብርተኝነትና መሰል ስጋቶችን ለመዋጋት ከፍተኛ የትብብር አቅም እንደሚሆን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የቀይ ባሕርና ኤደን ባሕረ ሰላጤ ሉዓላዊ መዳረሻ ፍላጎትና ጥያቄም ዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደኅንነትን በማረጋገጥ ለቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ብልፅግና የላቀ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል።

የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ በበኩላቸው፤ የቀይ ባሕርና ኤደን ባሕረ ሰላጤን ዘላቂ ሰላምና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማሳለጥ ሁሉንም ሀገራት የሚያሳትፍ የባሕር ላይ አስተዳደር መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል።


የኢትዮጵያ አስተማማኝ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄም ቀጣናዊ ትስስርን በማጎልበት በጋራ ተጠቃሚነት መርህ የተመሰረተ መሆኑን አስረድተዋል።

ለዚህም የንግድ መዳረሻ ወደቦችን ኢኮኖሚያዊ አስተሳሳሪ ሰንሰለትነት የሚያገለግሉበትን ወሳኝ የውሃ ላይ የአስተዳደር ሥርዓት መፍጠር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

በውይይቱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዩች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ኖጎ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ተጋባዥ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026