🔇Unmute
አዳማ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ ለዘንድሮ የትንሣዔ በዓል የተሻለ የእርድ እንስሳትና ሌሎች የፍጆታ ዕቃ አቅርቦት መኖሩን ሸማቾችና ነጋዴዎች ገለጹ።
በአዳማ እሮብ የእንስሳት ገበያ ሲገበያዩ ካገኘናቸው ሸማቾች መካከል አቶ ፍቅሬ ለማ በሰጡት አስተያየት በከተማዋ ለትንሣዔ በዓል በቂ የእርድ እንስሳት መኖሩን ይገልጻሉ።
አንድ መካከለኛ ሠንጋ በ90 ሺህ ብር መግዛታቸውን የተናገሩት አቶ ፍቅሬ፤ ካለፈው የበዓል ገበያ ጋር ሲነጻጸር በደለቡ ሰንጋዎች ላይ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ የታየበት መሆኑን ነው ያስረዱት።

ሌላኛው ሸማች አቶ ተሾመ ቱፋ በበኩላቸው ለዘንድሮው የትንሣኤ ገበያ ካለፉት ዓመታት በተለየ መልኩ ሰፊ የእንስሳት አቅርቦት የታየበት ነው ብለዋል።

ዋጋውም ቢሆን ተመጣጣኝ ነው ያሉት አስተያየት ሰጪው፤ እሳቸው ከስደስት ጓደኞቻቸው ጋር አንድ መጠነኛ በሬ በ80 ሺህ ብር መግዛታቸውን ገልጸዋል።
ሌሎች ሸማቾችም የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦት በተሻለ ሁኔታ መኖሩን ጠቅሰው አንድ ሠንጋ በሬ እስከ 160 ሺህ ብር ጥሪ መኖሩን ተናግረዋል።
ከሠንጋ ነጋዴዎች መካከል አቶ ታደሰ ፈይሳ በበኩላቸው፤ ለበዓሉ በቂ አቅርቦት በመኖሩ ገበያው የተረጋጋ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን ላይ ያለው የእርድ እንስሳት ዋጋ ከባለፈው ገና በዓል ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።
በአዳማ ቦሎ ገበያ ዶሮ እና እንቁላል ሲገበያዩ ያገኘናቸው አቶ ደበበ ፍቃዱ ለበዓሉ በቂ የዶሮ አቅርቦት እንዳለ ጠቅሰው እሳቸው ሁለት ዶሮዎችን መግዛታቸውን ተናግረዋል።

የዶሮ ነጋዴ አበራ መክቴ በበኩላቸው፤ ለበዓሉ በቂ አቅርቦት በመኖሩ ሁሉም ባለው አቅም መርጦ በመግዛት በዓሉን እንዲያከብር ያስችለዋል ብለዋል።
አሁን ላይ አንድ ዶሮ ከ 1 ሺህ 500 እስከ 2 ሺህ ብር ዋጋ መቅረቡን ጠቅሰው ይህም ዋጋ ካለፉት በዓላት ጋር ሲነጻጸር ተመጣጣኝ መሆኑን አስረድተዋል።
የአዳማ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ከድጃ ጀማል፤ በከተማዋ የሚገኙ የእንስሳት ገበያዎች የበግ፣ የፍየል፣ እንዲሁም የቀንድ ከብት አቅርቦት የተሟላ እንዲሆን አስቀድሞ መሰራቱን ገልጸዋል።

ለእርድ እንስሳት ንግድ መሳለጥም አዲስ የእንስሳት ገበያ በቦሌ ክፍለ ከተማ ጎሮ ወረዳ መከፈቱን ጠቅሰው ህብረተሰቡ በአቅራቢያው በሚገኙ ገበያዎች መጠቀም እንደሚችልም አስታውቀዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026