የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከለውጡ ወዲህ ለቱሪዝም ተኮር የቅርስ ልማት የተሰጠው ትኩረት የኢትዮጵያን ቱሪዝም ወደ አዲስ ምዕራፍ እያሸጋገረ ነው

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፦መንግሥት ለቱሪዝም ተኮር የቅርስ ጥበቃና ልማት የሰጠው ልዩ ትኩረት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እንድትሆን በማድረግ ለዘርፉ ዕድገት የጎላ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት መንግሥት ለቱሪዝም ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረትና በነደፈው የብዝኃ ዘርፍ ፖሊሲ አማካኝነት፣ ለዘመናት የተዘነጉ በርካታ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶች ተገቢውን ጥገናና እድሳት አግኝተው ለጎብኚዎች ክፍት ሆነዋል።


የጎንደር አብያተ መንግሥታት፣ ብሔራዊ ቤተ መንግሥት፣ ጂማ አባ ጅፋር ቤተ መንግሥት፣ ሐረር ጀጎል ግንብ፣ ሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በአዲስ አበባና ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶች ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ ታድሰው ለጎብኝዎች ክፍት ሆነዋል።

የኢትዮጵያ የቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት፣ መንግሥት ዘርፉን ለማሳደግ በወሰደው ቁርጠኝነት ቋሚና ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን የማልማት ተግባር በውጤታማነት እየተከናወነ ይገኛል።

በተለይም ለባህልና የከተማ ቱሪዝም ትኩረት በመሰጠቱ ተጨባጭ ለውጦች መመዝገቡን በማንሳት፥ የኢትዮጵያ የቅርስ ልማት ሥራ የቱሪዝም ዘርፉን ወደ አዲስ ምዕራፍ እያሸጋገረ ነው ብለዋል።

በለውጡ ዓመታት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጨምሮ የኢትዮጵያን ክብርና ታሪክ ከቱሪዝም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞችም መገንባታቸውን ገልጸዋል።

የቅርስ ቦታዎችን የማዘመን ስራ የኢትዮጵያን ገጽታ ከመገንባቱ ባለፈ፣ የጎብኝዎችን ቁጥር በመጨመር የቱሪዝም ገቢን ማሳደጉንና ለዜጎች ሰፊ የስራ ዕድል መፍጠሩን አንስተዋል።

ቅርሶች በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ የተደረገው ጥረት ለሀገሪቱ ታሪካዊ እሴቶች ተገቢውን ክብር አስገኝቷል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 19 ቅርሶችን በዩኔስኮ በማስመዝገብ በአፍሪካ ቀዳሚ ሥፍራ መያዟን ረዳት ፕሮፌሰር አበባው ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅትም ቋሚና የማይዳሰሱ ቅርሶችን የማስመዝገብ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አስታውቀዋል።


ከማይዳሰሱ ቅርሶች መካከልም የአገው ፈረስ ባህል፣ የሀላባ የዘመን መለወጫ 'ሴራ' እንዲሁም ዋዛ የሙዚቃ መሳሪያ ጨዋታ (ዙምባራ) በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ ቀርበዋል ነው ያሉት።

የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸውና አስቸኳይ ጥበቃ የሚያስፈልጋቸውን ቅርሶች ለመጀመሪያ ጊዜ ለማስመዝገብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በጣና ሐይቅ የሚገኙ ደሴቶችንና የአልነጃሺ ታሪካዊ መንደርን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ የተጀመሩ ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ቀደም ሲል በዩኔስኮ የሚመዘገቡ ቅርሶች ትኩረት ያደረገው የባህል ቅርሶች ላይ መሆኑን አንስተው በአሁኑ ወቅትም የተፈጥሮ ቅርሶችን ለማስመዝገብ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026