የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ያሳየችው ፈጣን ሽግግር እና ያስመዘገበችው ውጤት ለአህጉሪቱ  ምሳሌ ነው

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ያሳየችው ፈጣን ሽግግርና ያስመዘገበችው ውጤት ለአህጉሪቱ ምሳሌ መሆኑን በአፍሪካ ስታትስቲክስ ኢንስቲትዩት የኢኮኖሚ ስታትስቲክስ ዳይሬክቶሬት ኃላፊ አዱም ጋጎሉም ገለጹ።

ኃላፊው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፣ ከአህጉሪቱ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 65 በመቶውን አስተዋጽኦ የሚያደርገውን መደበኛ ያልሆነ የኢኮኖሚ ዘርፍ ለመደገፍ ዲጂታላይዜሽን ወሳኝ ነው።


በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን የፋይናንስ ተጠቃሚ ያደረጉት እንደ ቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብር ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ያመጡት ለውጥ እጅግ አስደናቂና አበረታች መሆኑን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለመክፈት የጀመረችው ስራ ለአህጉሪቱ አዲስ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲዎች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተለይም ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነትን ለማስፈን እንደ ቴሌኮም እና ባንክ ያሉ ቁልፍ ዘርፎች ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጋቸው የሀገሪቱን የሊብራላይዜሽን ጉዞ የሚያፋጥን ትክክለኛ ውሳኔ ነው ብለዋል።

የተመዘገቡት የልማት ስኬቶችና የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ በፈረንጆቹ 2063 የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚኖራቸው አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ እያሳየች ያለው ፈጣን ለውጥ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ከቀጠለ፣ አፍሪካ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነትና ክብር ከፍ እንደሚያደርገው አብራርተዋል።


የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የስታትስቲክስ ዲፓርትመንት ምክትል ዳይሬክተር ጂም ቴብራክ፣ ዲጂታላይዜሽን የፋይናንስ ተደራሽነትን በማስፋት ለዓለም ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።።

በኢትዮጵያ በዲጂታላይዜሽን መስፋፋት እየታየ ያለው እንቅስቃሴ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት ዓለም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘመን ላይ በመሆኗ፣ ሀገራት በጤና፣ በትምህርትና በንግድ ዘርፎች ተጠቃሚ ለመሆን አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህ የዲጂታል ለውጥ የፋይናንስ አገልግሎት ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ጭምር ቀላልና ፈጣን አማራጮችን በማስፋፋት፣ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ነው ያብራሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026