የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ትልቅ ማሳያ ነው

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2018 (ኢዜአ)፦ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ጸጋን የመለየት፣ የማልማትና ወደ ሀብት የመቀየር ትልቅ ማሳያ መሆኑንና ለወሎ የብልጽግና ተስፋ እንደሆነ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሣሽነት እና በ"ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር የተገነባውን የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ዛሬ በታሪካዊቷ የሐይቅ ከተማ ተገኝተው ሥራ ያስጀመሩት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በምርቃቱ ሥነ ሥርዓት ላይ ከአካባቢው ማኅበረሰብና ከአፋር ወንድሞች ጋር በአንድነት በመገኘታቸው የተሰማቸውን ታላቅ ደስታ ገልጸዋል።


ወሎ የኅብር ምልክት መሆኗን የጠቀሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በዕለቱ ከአፋር ወንድሞች ጋር የታየው አብሮነት የኢትዮጵያን ውበትና ወንድማማችነት ይበልጥ የገለጠ መሆኑን አመልክተዋል።

ይህ ፕሮጀክት ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው የመደመር ዕሳቤ በተግባር የታየበት መሆኑን ገልጸው የመንግሥት ሐሳብ፣ የባለሀብቱ ታታሪነት እና የሕዝቡ ትጋት የተሰባጠረበት ድንቅ ውጤት መሆኑን አብራርተዋል።

ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ሌት ተቀን ጥበቃ ላደረጉ የመከላከያ፣ የፖሊስ እና የሚሊሻ አባላት፣ እንዲሁም ለአካባቢው አመራርና ሕዝብ የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።

ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ሪዞርቱን ውብ አድርገው ከመገንባት ባለፈ፣ ጫትን በምርጥ የአትክልትና ፍራፍሬ ዝርያ በመተካት ለውጥ በተግባር እንደሚመጣ ማሳየታቸውን ገልጸዋል።


በተጨማሪም ባለሀብቱ ለሐይቅ ከተማ የገነቡት ትምህርት ቤት ለትውልድ የሚተርፍ ተግባር መሆኑን በመልዕክታቸው ላይ ጠቅሰዋል።

ዛሬ የታየው ልማት የሰላም ውጤት መሆኑን ያመለከቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች ሰላማቸውን አጥብቀው እንዲጠብቁ አደራ ብለዋል።

በአንድነት እና በትጋት ከተሠራ ቀጣናው የዕድገትና የብልጽግና መዳረሻ መሆኑ እንደማይቀርም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026