የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከተማ አስተዳደሩ የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ ነው

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መተማ ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ከተማ አስተዳደሩ የማህበረሰቡ ቁልፍ ጥያቄ የሆነውን የመኖሪያ ቤት እጥረት ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ መሆኑንበምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ጽህፈት ቤት በማህበር ተደራጅተው ሲቆጥቡ ለነበሩና መስፈርቱን ላሟሉ 580 ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ዛሬ ሰጥቷል፡፡

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታረቀኝ አለማየሁ በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ የከተማ አስተዳደሩ የማህበረሰቡ ቁልፍ ጥያቄ የሆነውን የመኖሪያ ቤት እጥረት ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።


በዚህም በ32 ማህበራት በመደራጀት ሲቆጥቡ ለነበሩና ሌሎች መስፈርቶችን ላሟሉ 580 ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ መስጠቱን ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውል 9 ነጥብ 3 ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማዘጋጀት ለእያንዳንዱ ሰው 160 ካሬ ሜትር ቦታ ዛሬ ማስረከብ መቻሉን አስረድተዋል።

ለመሬት ካሳ ከ49 ሚሊዮን ብር በላይ በመክፈል ከ3ኛ ወገን ነጻ በማድረግ ማስረከቡን ጠቁመው እድሜያቸው ለደረሰ የልማት ተነሺ ልጆችም የቤት መስሪያ ቦታ መሰጠቱን ተናግረዋል።

እያንዳንዱ የማህበር አባል በተሰጠው ቦታ ላይ በተሰጠው ጊዜ ገደብ ውስጥ ፈጥኖ ወደ ስራ በመግባትና አካባቢውን በማልማት የሚጠበቅበትን ሃላፊነት እንዲወጣም አሳስበዋል።


የገንዳውኃ ከተማ ነዋሪ አቶ ሽፈራው አለነ፤ የከተማ አስተዳደሩ የቤት መስሪያ ቦታ በመስጠት የዘመናት ጥያቄያቸውን ዛሬ እንደፈታላቸው ገልጸዋል።

በተሰጣቸው ቦታ ላይ ቤት ፈጥነው በመገንባት ሃብት ለመፍጠርና አሁን ካሉበት የቤት ኪራይ ችግር ለመላቀቅ ተግተው እንደሚሰሩም ተናግረዋል።

ሌላኛው የቤት መስሪያ ቦታ ተጠቃሚ የሆኑት አቶ አታለለ መርሻ በበኩላቸው፤ የብዙ ጊዜ ችግር የነበረውን የመኖሪያ ቦታ ይሰጠኝ ጥያቄ በመፈታቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል።

መንግስት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀው በተሰጣቸው ቦታ ላይ በተባለው ጊዜ ቤት ገንብተው ለማጠናቀቅ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።

በቦታ ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ የማህበር አባላትና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026