የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር አጋርነቱን ለማስቀጠል ያለውን ቁርጠኝነት አረጋገጠ

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2018(ኢዜአ)፦ የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኝነቱን ገለጸ።

ዓመታዊው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብስባ በዋሺንግተን ዲሲ መካሄዱን ቀጥሏል።

በገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የተመራው የኢትዮጵያ መንግሥት ልዑክ፣ ከስብስባው ጎን ለጎን ከሳዑዲ የልማት ፈንድ (SDF) ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሱልጣን አብዱልራህማን አል-ማርሻድ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርጓል።

በስብሰባው ወቅት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እና በሳዑዲ የልማት ፈንድ መካከል ያለውን ጠንካራ እና እያደገ የመጣ አጋርነት አድንቀዋል።


ሚኒስትሩ የመንግሥትን ቀጣይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ በአጽንኦት ያነሱ ሲሆን፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ድጋፍ የሚሹ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የኢንቨስትመንት ዘርፎችም አብራርተዋል።

ለስትራቴጂካዊ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ በተለይም ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሊቀርብ የሚችል ፋይናንስን እንዲሁም የኢኮኖሚ ዕድገት እና ቀጣናዊ ትስስርን ለመደገፍ የሚደረገውን የመንገድ ትስስር ማስፋፊያን ያካተቱ ሀሳቦች በውይይቱ ላይ ተነስተዋል።

ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለምትሰጣቸው የልማት ጉዳዮች ስኬታማነት ቀጣይነት ያለው ትብብር ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።

ሱልጣን አብዱልራህማን አል-ማርሻድ በበኩላቸው የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ነው ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ቁልፍ የሆኑ የኢትዮጵያ የልማት ኢኒሼቲቮች ለመደገፍ ትብብሩን ይበልጥ ለማጠናከር ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026