🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2018(ኢዜአ)፦ የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኝነቱን ገለጸ።
ዓመታዊው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብስባ በዋሺንግተን ዲሲ መካሄዱን ቀጥሏል።
በገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የተመራው የኢትዮጵያ መንግሥት ልዑክ፣ ከስብስባው ጎን ለጎን ከሳዑዲ የልማት ፈንድ (SDF) ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሱልጣን አብዱልራህማን አል-ማርሻድ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርጓል።
በስብሰባው ወቅት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እና በሳዑዲ የልማት ፈንድ መካከል ያለውን ጠንካራ እና እያደገ የመጣ አጋርነት አድንቀዋል።

ሚኒስትሩ የመንግሥትን ቀጣይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ በአጽንኦት ያነሱ ሲሆን፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ድጋፍ የሚሹ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የኢንቨስትመንት ዘርፎችም አብራርተዋል።
ለስትራቴጂካዊ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ በተለይም ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሊቀርብ የሚችል ፋይናንስን እንዲሁም የኢኮኖሚ ዕድገት እና ቀጣናዊ ትስስርን ለመደገፍ የሚደረገውን የመንገድ ትስስር ማስፋፊያን ያካተቱ ሀሳቦች በውይይቱ ላይ ተነስተዋል።
ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለምትሰጣቸው የልማት ጉዳዮች ስኬታማነት ቀጣይነት ያለው ትብብር ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
ሱልጣን አብዱልራህማን አል-ማርሻድ በበኩላቸው የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ነው ብለዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው ቁልፍ የሆኑ የኢትዮጵያ የልማት ኢኒሼቲቮች ለመደገፍ ትብብሩን ይበልጥ ለማጠናከር ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026