የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር አጋርነቱን ለማስቀጠል ያለውን ቁርጠኝነት አረጋገጠ

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2018(ኢዜአ)፦ የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኝነቱን ገለጸ።

ዓመታዊው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የፀደይ ወቅት ስብስባ በዋሺንግተን ዲሲ መካሄዱን ቀጥሏል።

በገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የተመራው የኢትዮጵያ መንግሥት ልዑክ፣ ከስብስባው ጎን ለጎን ከሳዑዲ የልማት ፈንድ (SDF) ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሱልጣን አብዱልራህማን አል-ማርሻድ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርጓል።

በስብሰባው ወቅት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እና በሳዑዲ የልማት ፈንድ መካከል ያለውን ጠንካራ እና እያደገ የመጣ አጋርነት አድንቀዋል።


ሚኒስትሩ የመንግሥትን ቀጣይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ በአጽንኦት ያነሱ ሲሆን፣ ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ድጋፍ የሚሹ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የኢንቨስትመንት ዘርፎችም አብራርተዋል።

ለስትራቴጂካዊ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ በተለይም ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሊቀርብ የሚችል ፋይናንስን እንዲሁም የኢኮኖሚ ዕድገት እና ቀጣናዊ ትስስርን ለመደገፍ የሚደረገውን የመንገድ ትስስር ማስፋፊያን ያካተቱ ሀሳቦች በውይይቱ ላይ ተነስተዋል።

ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለምትሰጣቸው የልማት ጉዳዮች ስኬታማነት ቀጣይነት ያለው ትብብር ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።

ሱልጣን አብዱልራህማን አል-ማርሻድ በበኩላቸው የሳዑዲ የልማት ፈንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ነው ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ቁልፍ የሆኑ የኢትዮጵያ የልማት ኢኒሼቲቮች ለመደገፍ ትብብሩን ይበልጥ ለማጠናከር ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026