የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሰራተኞችን የስራ ባህል አሻሽሏል

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የሰራተኞችን የስራ ባህል ማሻሻሉን የአገልግሎቱ ስራ አስኪያጅ ገለጹ።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ መኩሪያ ድንቁ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በከተማው 138 አገልግሎቶች በመሶብ አንድ ማዕከል ውስጥ እየተሰጡ ነው።

በዚህም 31 የሚሆኑ የአስተዳደሩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ የተቀናጀ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል።

በማዕከሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የተቀናጀ ፈጣን አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እየተቻለ መሆኑን ጠቁመው፤ ለተገልጋዮችም ምቹና ፅዱ በሆነ አካባቢ አገልግሎት ማግኘት ማስቻሉን ተናግረዋል።

የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩ የሰራተኞችን የስራ ባህል ከመለወጡም ባለፈ የመንግስት የስራ ሰዓትን በአግባቡ የመጠቀም ዝንባሌ እየጨመረ መምጣቱንም ገልጸዋል።

በማዕከሉ 18 የሚሆኑ የለሙ ቴክኖሎጂዎች በተሟላ መልኩ የኦንላይን አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የገለጹት ሃላፊው፤ የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሠራተኞችን አቅም በቴክኖሎጂ የማብቃት ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።

በከተማዋ ደረጃ ካለው ማዕከል ባለፈ በዳቤ፣ በአባ ገዳና በቦሌ ክፍለ ከተሞች የአንድ ማዕከል አገልግሎቱን ማስፋፋት ተችሏል ብለዋል።

በአዳማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሲገለገሉ ያገኘናቸው አቶ አብረሃም ወይሴ፤ ለመሬት ጉዳይ አገልግሎት ለማግኘት ፈልገው መምጣታቸውን ገልጸዋል።


የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት ችግሮች እንደነበሩ አንስተው፤ በተለይ ከአንድ መስሪያ ቤት ወደ ሌላው የሚደረገው ጉዞ እና ምልልስ ፈታኝ እንደነበር ጠቅሰዋል።

በአሁኑ ወቅት ሁሉንም አገልግሎት በአንድ መስኮት እያገኘን ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ወይዘሮ አለምነሽ ሽብሩ በበኩላቸው "ከበር ጀምሮ ያለው አቀባበልና ማስተናገጃው በጣም ደስ የሚል ነው" በማለት ይገልጻሉ።


በምቹ ማዕከል የተቀላጠፈ አገልግሎት በማግኘታቸው መደሰታቸውንም ተገልጋዮቹ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026