የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የሲዳማ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ተናገሩ።

የከተማዋ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማጠናቀቂያ የምስጋናና ዕውቅና እንዲሁም የአራተኛ ዙር የኮሪደር ልማትና የሐይቅ ዳርቻ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄዷል፡፡


በመርሀ ግብሩ ላይም የሲዳማ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሀም ማርሻሎ ‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በከተማዋ ተጠናቀው ለአገልግሎት በበቁ የሁለተኛ እና ሶስተኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራዎች የተሳተፉ አመራርና ባለሙያዎችን፣ የሥራ ተቋራጮችን እና በተለያየ መንገድ አስተዋፅኦ ያደረጉ የህብረተሰብ ክፍሎችን አመስግነዋል፡፡

ባለፉት የኮሪደር ልማት ሥራዎች እነዚህ አካላት፣ ልምዳቸውን፣ ዕውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውንና ጉልበታቸውን በማስተባበር በቁጭት መስራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ከተማዋ በሀገር እንዲሁም በአፍሪካ ደረጃ ተመራጭና ተወዳዳሪነቷ እንዲጨምር በቀጣይ ለሚከናወነው የኮሪደር እና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ስራ ርብርባቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡


ዕውቅና ከተሰጣቸው የሥራ ተቋራጮች መካከል የይርጋዓለም ኮንስትራክሽን ባለቤት ወይዘሮ ይርጋዓለም አስፋው የተሰጣቸው ዕውቅና በቀጣይ ሥራዎች ላይ የላቀ ሥራ ለመስራት እንደሚያተጋቸው ተናግረዋል፡፡

በግል አስተዋፅዖ እውቅና ከተሰጣቸው የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ጋሻው ምትኬ (ዶ/ር) በበኩላቸው በተለይ በአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ላይ የአፈር አይነት መረጣ፣ የሚተከሉ ዕፅዋት ልየታ እና እንክብካቤ እንዲሁም ከዚህ ጋር የተያያዙ ሌሎች ሙያዊ አበርክቶዎችን ያለክፍያ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ ከተማዋ አምራና ደምቃ ሲመለከቷት የህሊና እርካታ እንደሚሰማቸው ጠቅሰው ለከተማቸው በዚህ መልኩ ሙያዊ ተሳትፎ ማድረጋቸውን እንደ እድለኝነት እንደሚቆጥሩት ነው የተናገሩት፡፡

‎አራተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ከ3 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር በላይ እንደሚሸፍን የተገለጸ ሲሆን በከተማዋ በሚገኘው የፍቅር ሀይቅ ዙሪያ የሚከናወነው የሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ስራ በመጠናቀቁ በቅርቡ ወደ ግንባታ እንደሚገባም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026