🔇Unmute
ሃዋሳ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦-የሕብረት ሥራ ማህበራት በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ የሚኖራቸውን ሚና ለማሳደግ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን “ወደ ቀበሌ መድረስ” በሚል መሪ ሃሳብ 2ኛውን ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ሪፎርም የንቅናቄ መድረክ በተለያዩ ከተሞች በማካሄድ ላይ ይገኛል።

በሀዋሳ እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)፤ ከተናጠል ጥረት በሕብረት በተደመረ አቅም የሚከናወኑ ተግባራት ለሀገል ልማትና እድገት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም መሰረት በለውጡ ዓመታት የሕብረት ሥራ ማህበራት በሀገር ልማትና የምጣኔ ሃብት እድገት ላይ የላቀ ሚናቸውን እንዲወጡ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል፤ በዚህም ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።
ሕብረት ሥራ ማህበራት የአስተሳሰብ፣ የአደረጃጀት፣ የአሰራርና የአመራር ሪፎርም ካደረጉ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት የሚችሉ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም በቀጣይ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ የሚኖራቸውን ሚና ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
የሕብረት ሥራ ማህበራት የኢትዮጵያን እድገትና ማንሰራራት ለማስቀጠል ወሳኝ መሆናቸውን በማንሳት ቀጣይነት እንዲኖራቸው መሰል ንቅናቄዎች ያስፈልጋሉ ብለዋል።

የፌዴራል ሕብረት ሥራ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሺሰማ ገብረስላሴ፤ የሕብረት ሥራ ማህበራትን አቅም በማሳደግ ለሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ የሚኖራቸውን አስተዋጽኦ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም በሀዋሳ፣ አዳማ፣ ጅማ፣ ጅግጅጋ፣ አሶሳና ኮምቦልቻ ከተሞች በዛሬው እለት ተመሳሳይ መድረኮች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው በሌሎችም ይቀጥላል ብለዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026