🔇Unmute
ጅማ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ ህብረት ስራ ማህበራት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲደርሱ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት እየመጣ መሆኑን የኢትዮጵያ የህብረት ስራ ኮሚሽን ገለጸ።
ሁለተኛው ዙር "ቀበሌ የመድረስ ምዕራፍ" ሀገር አቀፍ የህብረት ስራ ሪፎርም ንቅናቄ በዛሬው ዕለት በስድስት ክላስተሮች መሰጠት ተጀምሯል።
የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን የህብረት ስራ ኦዲት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ጠሀ ዲጋ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ መሠረታዊ የህብረት ስራ ማህበራት ዘመናዊ መሆንና መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት ለሀገር ኢኮኖሚ ጠንካራ መሠረት ነው።
ቀደም ሲል የማህበራቱ አደረጃጀት በፅኑ መሠረት ላይ ባለመሆኑ ቀጣይነታቸው ጥያቄ ውስጥ ሲገባ እንደነበር አስታውሰው፣ አሁን እየተተገበረ ባለው ሪፎርም ተስፋ ሰጪ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ መድረክ በዋናነት በማህበራቱ አመራርና ባለሙያዎች ዘንድ የአመለካከትና የእውቀት ለውጥ ለማምጣት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የጅማ ዞን የህብረት ስራ ማህበራት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ድማሙ ንጋቱ በበኩላቸው፤ የህብረት ስራ ማህበራት የሀገሪቱን የልማት ጉዞ በማፋጠን ረገድ ያላቸው ሚና የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም የፋይናንስ ተቋማት ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱ ለማህበራቱ መጠናከር ትልቅ ድርሻ ማበርከቱን ገልጸዋል።
በጅማ ከተማ እየተካሄደ ባለው በዚህ ንቅናቄ ከጋምቤላ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ከኦሮሚያ ክልሎች የተውጣጡ 400 የህብረት ስራ ማህበራት የልማት ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026