የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያለ እንግልት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለማግኘት አስችሎናል

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያለ እንግልት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለማግኘት አስችሎናል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በማዕከሉ የንግድ ፈቃዳቸውን ለማሳደስ የተገኙት አቶ መሐመድ ሁሴን፤ ያለ እንግልት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለማግኘት መቻላቸውን ነው የሚገልጹት።


አገልግሎቱ ከወረቀት ንኪኪ የጸዳ ከመሆኑም ባሻገር ቀልጣፋና የደንበኞችን ክብር በጠበቀ መንገድ የሚከናወን መሆኑም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።

ይህም መንግሥት መልካም አስተዳደር ለማስፈን እና የሕዝብ እንግልትን ለመቀነስ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑን ገልጸዋል።

ወይዘሮ እርጎዬ ሽፈራሁ የተባሉ ተገልጋይ በበኩላቸው በማዕከሉ እንግልት ሳይኖር በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ነው የሚገልጹት።


በመሶብ የአንድ ማዕከል በአንድ ቦታ ጊዜና ገንዘብን ቆጥቦ ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት በመቻላቸው ከእንግልት መዳናቸውን ነው ያመለከቱት።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በማውጣት ላይ የነበረው ወጣት ኤልያስ አዘነ በበኩሉ፤በወራት ቀጠሮ የማያልቁ ጉዳዮችን በደቂቃዎች መጨረስ እየተቻለ በመሆኑ ቴክኖሎጂውን በተሻለ መንገድ በማልማት አገልግሎቱን አስተማማኝ ማድረግ የሚያስፈልግ መሆኑን አመላክቷል።


የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የቴክኖሎጂ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አሕመድ ሁሴን፤ በማዕከሉ በአምስት ወራት ብቻ ከ22 ሺ ለሚበልጡ ዜጎች አገልግሎት መስጠት ተችሏል ብለዋል፡፡

ከተገልጋዮች በሲስተም የተወሰደ የጥናት መረጃ እንደሚያመለክተውም የደንበኞች እርካታ መጠንን 97 ነጥብ 8 በመቶ ለማድረስ መቻሉን ገልፀዋል።


በክልሉ ለዜጎች ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ጠንካራ የዲጂታላይዜሽን ሲስተም የመገንባቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የሚዛን አማን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋም ውስጥ 9 የክልልና የፌዴራል ተቋማት 38 አገልግሎቶቻቸውን እንዲሰጡ ተደርጎ የተደራጀ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026