የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያለ እንግልት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለማግኘት አስችሎናል

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያለ እንግልት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለማግኘት አስችሎናል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በማዕከሉ የንግድ ፈቃዳቸውን ለማሳደስ የተገኙት አቶ መሐመድ ሁሴን፤ ያለ እንግልት የተለያዩ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ለማግኘት መቻላቸውን ነው የሚገልጹት።


አገልግሎቱ ከወረቀት ንኪኪ የጸዳ ከመሆኑም ባሻገር ቀልጣፋና የደንበኞችን ክብር በጠበቀ መንገድ የሚከናወን መሆኑም እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።

ይህም መንግሥት መልካም አስተዳደር ለማስፈን እና የሕዝብ እንግልትን ለመቀነስ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑን ገልጸዋል።

ወይዘሮ እርጎዬ ሽፈራሁ የተባሉ ተገልጋይ በበኩላቸው በማዕከሉ እንግልት ሳይኖር በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን ነው የሚገልጹት።


በመሶብ የአንድ ማዕከል በአንድ ቦታ ጊዜና ገንዘብን ቆጥቦ ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት በመቻላቸው ከእንግልት መዳናቸውን ነው ያመለከቱት።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በማውጣት ላይ የነበረው ወጣት ኤልያስ አዘነ በበኩሉ፤በወራት ቀጠሮ የማያልቁ ጉዳዮችን በደቂቃዎች መጨረስ እየተቻለ በመሆኑ ቴክኖሎጂውን በተሻለ መንገድ በማልማት አገልግሎቱን አስተማማኝ ማድረግ የሚያስፈልግ መሆኑን አመላክቷል።


የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የቴክኖሎጂ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አሕመድ ሁሴን፤ በማዕከሉ በአምስት ወራት ብቻ ከ22 ሺ ለሚበልጡ ዜጎች አገልግሎት መስጠት ተችሏል ብለዋል፡፡

ከተገልጋዮች በሲስተም የተወሰደ የጥናት መረጃ እንደሚያመለክተውም የደንበኞች እርካታ መጠንን 97 ነጥብ 8 በመቶ ለማድረስ መቻሉን ገልፀዋል።


በክልሉ ለዜጎች ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ጠንካራ የዲጂታላይዜሽን ሲስተም የመገንባቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የሚዛን አማን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋም ውስጥ 9 የክልልና የፌዴራል ተቋማት 38 አገልግሎቶቻቸውን እንዲሰጡ ተደርጎ የተደራጀ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026