የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ የዜጎችን የፈጠራ ክህሎትና የስታርት አፕ ተወዳዳሪነት እያጎለበተ ነው

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ ሀገር በቀል ዕውቀትን በማበረታታት የዜጎች የፈጠራ ክህሎትና የስታርት አፕ ተወዳዳሪነት እንዲጎለብት ማድረጉን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል።

በማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክትም፤ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለቀጣዩ የዕድገት ምዕራፍ ዋነኛ ምሰሶ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ትልም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶችን በማስፋት የስታርት አፕ ፈጠራን የማበረታታት ተግባር ቁልፍ ተግባር እንደሆነ አስገንዝበዋል።

በዛሬው ዕለትም ኮከብ የተሰኘ የዲጂታል ፕላትፎርም የሕጻናትን ዝንባሌ የሚመጥን ሳቢ የመማሪያ የዲጂታል ሥርዓት ይፋ አድርጓል።


በዚሁ ወቅት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የቴክኖሎጂ አማካሪ ሻምበል ይልማ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያን ዕድገት ለማሳለጥ ፈጠራን ማበረታታት ወሳኝ ነው ብለዋል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂክ አቅጣጫም ሀገር በቀል ዕውቀትን በማበረታታት የዜጎች የፈጠራ ክህሎትና ስታርት አፕ ተወዳዳሪነት እንዲጎለብት ማድረጉን ገልጸዋል።

የፈጠራ ክህሎት ማበረታቻ የሕግና የፖሊሲ አቅጣጫም ሀገር በቀል ዕውቀትን በማጎልበት የዲጂታል ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኮከብ ዲጂታል ፕላትፎርም መምህራንና ተማሪዎችን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ የፖሊሲ አቅጣጫ ተግባራዊ ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል።


የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ጥላዬ ዘውዴ፤ ዲጂታል ክህሎትን በአዎንታዊ መንገድ በማጎልበት የልማት ማሳለጫ አቅም ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ የትምህርት ሥርዓትን ማጠናከር የተማሪዎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማጎልበት የላቀ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

የኮከብ ዲጂታል ፕላትፎርምንም የትምህርት ባለድርሻ አካላት የሕጻናትን የዲጂታል ክህሎት ማበልጸግ በሚያስችል መልኩ መጠቀም እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።


የኮከብ ዲጂታል ፕላትፎርም መስራች ማህሌት ስዩም በበኩላቸው፤ መተግበሪያው ዕድሜያቸው ከ10 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትን የንባብ ባህል ለማዳበር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አስታውቀዋል።

ይህም መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት መነሻ በማድረግ የታዳጊዎችን የፈጠራ ተነሳሽነት የሚያሳድግ ወሳኝ የፈጠራ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026