የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የቅርስ ጥበቃ እና ልማት ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው ሚና አድጓል

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ለቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ዘርፉ ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው ድርሻ ማደጉን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ገለጹ።


3ኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር በዲጂታል ዘመን በሚል መሪ ሐሳብ መካሄድ ጀምሯል።

ሚኒስትር ዴዔታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የለውጡ መንግሥት በቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራን በተመለከተ ልዩ ትኩረት በመስጠቱ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል።


ቅርሶች የውጭ ምንዛሪን በማስገኘት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም ለአርኪዎሎጂስቶችና ለታሪክ ተመራማሪዎች የማይነጥፍ የመረጃ ምንጭ ሆነው እያገለገሉ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

ቅርሶች ተጠብቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ የማድረግ፣ የቅርስ አያያዝንና አጠቃቀምን የማዘመን ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


የቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራው ዲጂታላይዝ እየተደረገ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረ/ፕ) ናቸው።


ጉባዔው በቅርስ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን መርምሮ መፍትሔ ለመስጠትና አዳዲስ ዕውቀቶችን ለመለዋወጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026