የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በሐረሪ ክልል ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወስደዋል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ገለጸ።

የሐረሪ ክልል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ሃላፊና የክልሉ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አስተባባሪ ሳዳም መሐመድ እንደገለጹት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በክልሉ የከተማና ገጠር ወረዳዎች ተደራሽ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው።

በዚህም ባለፉት 9 ወራት ብቻ ከ180 ሺህ በላይ ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውንና በአጠቃላይ በእስካሁኑ ሂደት ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውን ጠቅሰዋል።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መሳካት ጉልህ አበርክቶ አለው ሲሉም ገልጸዋል።

በተለይም የዲጂታል ማንነት መለያ ተቋማት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ በማስቻል ግልፅነትና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

መታወቂያው በአገልግሎት ሰጪና ተቀባዩ መካከል ይበልጥ መተማመን እንዲኖር የሚያስችል፣ የተቋማትን ሥራ የሚያቀናጅ፣ በግለሰቦች ደረጃም የራስን መብት የሚያስጠብቅ መሆኑንም አክለዋል።

በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባ ያላካሄዱ የማህበረሰብ ክፍሎችም በአቅራቢያቸው በሚገኙ የምዝገባ ማዕከላት አገልግሎቱን እንዲጠቀሙ ሃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026