የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በሐረሪ ክልል ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወስደዋል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መውሰዳቸውን የክልሉ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ገለጸ።

የሐረሪ ክልል ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ሃላፊና የክልሉ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አስተባባሪ ሳዳም መሐመድ እንደገለጹት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን በክልሉ የከተማና ገጠር ወረዳዎች ተደራሽ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው።

በዚህም ባለፉት 9 ወራት ብቻ ከ180 ሺህ በላይ ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውንና በአጠቃላይ በእስካሁኑ ሂደት ከ357 ሺህ በላይ ዜጎች መታወቂያውን መውሰዳቸውን ጠቅሰዋል።

ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መሳካት ጉልህ አበርክቶ አለው ሲሉም ገልጸዋል።

በተለይም የዲጂታል ማንነት መለያ ተቋማት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ በማስቻል ግልፅነትና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

መታወቂያው በአገልግሎት ሰጪና ተቀባዩ መካከል ይበልጥ መተማመን እንዲኖር የሚያስችል፣ የተቋማትን ሥራ የሚያቀናጅ፣ በግለሰቦች ደረጃም የራስን መብት የሚያስጠብቅ መሆኑንም አክለዋል።

በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባ ያላካሄዱ የማህበረሰብ ክፍሎችም በአቅራቢያቸው በሚገኙ የምዝገባ ማዕከላት አገልግሎቱን እንዲጠቀሙ ሃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026