የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በባሕር ዳር ከተማ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት ከ596 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተገኘ

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕር ዳር፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በበጋ መስኖ ከለማው መሬት ከ596 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።


በመምሪው የሆልቲካልቸር ዘርፍ የድኅረ ምርት ባለሙያ ኃይሉ መላክ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ 17 ሺህ 635 አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በተካሄደው የመስኖ ልማት 596 ሺህ 232 ኩንታል የስንዴ፣ የአትክልት፣ የቅመማ ቅመምና ሌሎች ሰብሎች ምርት ተገኝቷል።

ከዚህ ውስጥም በ6 ሺህ 140 ሔክታር ላይ ከለማው ማሳ የተገኘው 279 ሺህ 984 ኩንታል የስንዴ ምርት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል ብለዋል።


ከበጋ መስኖ የተገኘው ምርት ከዕቅዱም ሆነ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው ምርት በላይ መሆኑንም አስረድተዋል።

በአጠቃላይ የተገኘውን ምርትም ለገበያ በማቅረብ የአቅርቦት እጥረት እንዳይኖርና የዋጋ ንረት እንዳይባባስ መደረጉን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026