የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በባሕር ዳር ከተማ በበጋ መስኖ ከለማው መሬት ከ596 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ተገኘ

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕር ዳር፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በበጋ መስኖ ከለማው መሬት ከ596 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።


በመምሪው የሆልቲካልቸር ዘርፍ የድኅረ ምርት ባለሙያ ኃይሉ መላክ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ 17 ሺህ 635 አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በተካሄደው የመስኖ ልማት 596 ሺህ 232 ኩንታል የስንዴ፣ የአትክልት፣ የቅመማ ቅመምና ሌሎች ሰብሎች ምርት ተገኝቷል።

ከዚህ ውስጥም በ6 ሺህ 140 ሔክታር ላይ ከለማው ማሳ የተገኘው 279 ሺህ 984 ኩንታል የስንዴ ምርት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል ብለዋል።


ከበጋ መስኖ የተገኘው ምርት ከዕቅዱም ሆነ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው ምርት በላይ መሆኑንም አስረድተዋል።

በአጠቃላይ የተገኘውን ምርትም ለገበያ በማቅረብ የአቅርቦት እጥረት እንዳይኖርና የዋጋ ንረት እንዳይባባስ መደረጉን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026