🔇Unmute
ባሕር ዳር፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በበጋ መስኖ ከለማው መሬት ከ596 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪው የሆልቲካልቸር ዘርፍ የድኅረ ምርት ባለሙያ ኃይሉ መላክ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ 17 ሺህ 635 አርሶ አደሮችን በማሳተፍ በተካሄደው የመስኖ ልማት 596 ሺህ 232 ኩንታል የስንዴ፣ የአትክልት፣ የቅመማ ቅመምና ሌሎች ሰብሎች ምርት ተገኝቷል።
ከዚህ ውስጥም በ6 ሺህ 140 ሔክታር ላይ ከለማው ማሳ የተገኘው 279 ሺህ 984 ኩንታል የስንዴ ምርት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል ብለዋል።

ከበጋ መስኖ የተገኘው ምርት ከዕቅዱም ሆነ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው ምርት በላይ መሆኑንም አስረድተዋል።
በአጠቃላይ የተገኘውን ምርትም ለገበያ በማቅረብ የአቅርቦት እጥረት እንዳይኖርና የዋጋ ንረት እንዳይባባስ መደረጉን ጠቅሰዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026