🔇Unmute
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በክልሉ የሚሰበሰበው ግብር ለከተሞች የመሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው(ዶ/ር) ገለጹ።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች በባህር ዳር ከተማ እየተካሔደ ያለውን የኮሪደርና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።

የቢሮ ኃላፊው መንገሻ ፈንታው(ዶ/ር) በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚሰበሰበው ግብር የከተሞችንና የገጠሩን ሕዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማቶችን ለማሳለጥ እየዋለ ነው።
ለዚህም በባህር ዳር ከተማ የተገነቡት የኮሪደር ልማት፣ መሶብ አንድ ማዕከል፣ ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎች መዝናኛዎች ማረጋገጫ ናቸው ብለዋል።
የተገነቡት የመሰረት ልማት ስራዎችም የከተሞቹን ገጽታ በመቀየርና የህብረተሰቡን አኗኗር በማሻሻል ለውጥ ማምጣት ያስቻሉ መሆናቸውንም ነው ያመለከቱት።
በቀጣይም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ለክልሉ እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያረጋገጡት።
የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤በከተማዋ የኮሪደርና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካሔዳቸው የቱሪዝምና የኢንዱስትሪ ፍሰት እንዲጨመር አድርጓል።

ልማትን በተገቢው መንገድ ለማከናወን ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ አመልክተው ለዚህም የተቋሙ ሰራተኞች ይበልጥ በትጋት ሊሰሩ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት።
በጉብኝቱ የተሳተፉት ወይዘሮ ትዕግስት ዘሪሁን እንደገለጹት፤ ሰራተኛው የልማት ፕሮጀክቶችን እንዲጎበኝ መደረጉ ገቢን አሟጦ ከመሰብሰብ አኳያ በላቀ ተነሳሽነት እንዲሰራ የሚያደርግ ነው።

በከተማ እየተካሔዱ ያሉት የልማት ፕሮጀክቶች ከሕብረተሰቡ የሚሰበሰበው ገቢ ማሕበረሰቡን የመሰረተ ልማት ተጠቀሚ ለሚደረጉ የልማት ስራዎች መዋሉን የሚያረጋግጡ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራትም 69 ቢሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ማዋል መቻሉንም ነው ያስገነዘቡት።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026