🔇Unmute
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በክልሉ የሚሰበሰበው ግብር ለከተሞች የመሰረተ ልማት ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው(ዶ/ር) ገለጹ።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች በባህር ዳር ከተማ እየተካሔደ ያለውን የኮሪደርና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።

የቢሮ ኃላፊው መንገሻ ፈንታው(ዶ/ር) በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚሰበሰበው ግብር የከተሞችንና የገጠሩን ሕዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማቶችን ለማሳለጥ እየዋለ ነው።
ለዚህም በባህር ዳር ከተማ የተገነቡት የኮሪደር ልማት፣ መሶብ አንድ ማዕከል፣ ሰፋፊ የአስፋልት መንገዶች፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎች መዝናኛዎች ማረጋገጫ ናቸው ብለዋል።
የተገነቡት የመሰረት ልማት ስራዎችም የከተሞቹን ገጽታ በመቀየርና የህብረተሰቡን አኗኗር በማሻሻል ለውጥ ማምጣት ያስቻሉ መሆናቸውንም ነው ያመለከቱት።
በቀጣይም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ ለክልሉ እድገት ለማዋል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያረጋገጡት።
የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤በከተማዋ የኮሪደርና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መካሔዳቸው የቱሪዝምና የኢንዱስትሪ ፍሰት እንዲጨመር አድርጓል።

ልማትን በተገቢው መንገድ ለማከናወን ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ አመልክተው ለዚህም የተቋሙ ሰራተኞች ይበልጥ በትጋት ሊሰሩ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት።
በጉብኝቱ የተሳተፉት ወይዘሮ ትዕግስት ዘሪሁን እንደገለጹት፤ ሰራተኛው የልማት ፕሮጀክቶችን እንዲጎበኝ መደረጉ ገቢን አሟጦ ከመሰብሰብ አኳያ በላቀ ተነሳሽነት እንዲሰራ የሚያደርግ ነው።

በከተማ እየተካሔዱ ያሉት የልማት ፕሮጀክቶች ከሕብረተሰቡ የሚሰበሰበው ገቢ ማሕበረሰቡን የመሰረተ ልማት ተጠቀሚ ለሚደረጉ የልማት ስራዎች መዋሉን የሚያረጋግጡ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራትም 69 ቢሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ማዋል መቻሉንም ነው ያስገነዘቡት።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026