የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 35 ባለሀብቶችን ወደ ስራ አስገብቷል

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ፓርኮች ኮርፖሬሽን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 35 ባለሀብቶችን ተቀብሎ ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ገለጸ።

ኮርፖሬሽኑ በተለይ የገቢ ምርቶችን በሚተኩ የልማት ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራቱም ውጤታማ ጅምር መኖሩን አረጋግጧል።

በኮርፖሬሽኑ የልማት ዘርፍ ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰለሞን ቱፋ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኮርፖሬሽኑ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የማልማት ፣ የማስተዳደርና ገቢ የማመንጨት ተልዕኮውን በስኬት እየተወጣ ይገኛል።

በበጀት ዓመቱም ባለሀብቶች በቡልቡላ የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በመካከለኛ ኢንዱስትሪ ማዕከላት፣ ጥቃቅን ኢንዱስትሪ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ገቢን ለማመንጨትና ተኪ ምርቶችን ለማምረት ወደ ስራ መግባታቸውንም ነው የገለጹት።


ባለሀብቶቹ በዋናነት በምግብ ዘይት፣ በጥራጥሬና ፍራፍሬ ልማት እንዲሁም በተለያዩ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ላይ መሰማራታቸውን ተናግረዋል።

ባለሀብቶቹ ስራ የጀመሩት መሰረተ ልማት በተሟላላቸው ስፍራዎች መሆኑን የገለጹት አቶ ሰለሞን፣ በዋናነትም የቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በስሩ የሚገኙ 6 መካከለኛ ኢንዱስትሪ ማዕከላት መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በበጀት ዓመቱም 35 ባለሀብቶችን ወደ ማምረት ስራ ማስገባት በመቻሉ በአጠቃላይ የአልሚ ባለሀብቶች ቁጥር 81 ደርሷል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት በኮርፖሬሽኑ ስር በሚገኙ ፓርኮች ተመርቶ ለገበያ የቀረበ ሲሆን፣ ከዚህም 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል።


ወደ ስራ በገቡት አምራች ኢንዱስትሪዎች 3 ሺህ 225 ዜጎች የስራ ዕድል ማግኘታቸውንም አስታውቀዋል።

በነቀምቴ የተቀናጀ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከለማው 60 ሄክታር መሬት ውስጥ 10 ሄክታሩ ለባለሀብቶች የተላለፈ ሲሆን ከተገነቡት ሶስት ሼዶች መካከል ሁለቱ ለባለሀብቶች እንዲተላለፉ መደረጉንም ገልፀዋል።

ኮርፖሬሽኑ በቀጣይም የለሙ መሬቶችን በማቅረብና አምራቾች ምርቶቻቸውን በስፋት ለገበያ እንዲያቀርቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ምክትል ስራ አስፈጻሚው አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026