የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በዞኑ ቋሚ ፍራፍሬን በኩታ ገጠም በማልማት አርሶ አደሩን በዘላቂነት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ወሎ ዞን በኩታገጠም ቋሚ ፍራፍሬን በማልማት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በዞኑ እስከ ሐምሌ 30/2018 የሚዘልቅ 900 ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም እርሻ ፍራፍሬን ለማልማት የሚያስችል የችግኝ ተከላ ዘመቻ ተጀምሯል።

የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዞኑ የፍራፍሬ ችግኝ ተከላውን የሚያካሔደው ተስማሚ ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ባላቸው አምስት ወረዳዎች ነው።

በዚህ የዘመቻ ስራ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ሙዝ፣ ብርቱካንና ሌሎች ቋሚ የፍራፍሬ ችግኞችን የመትከል ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።


የችግኝ ተከላው በተሁለደሬ፣ በአምባሰል፣ በቃሉ፣ በወረባቦና በአርጎባ ብሔረሰብ ወረዳዎች እየተከናወነ ነው።

ይህም በዘልማድና በተበታተነ አግባብ የሚካሔዱ የፍራፍሬ ልማት ስራዎችን በማስቀረት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጥ፣ በሽታን የሚከላከልና ምርታማ የፍራፍሬ ችግኝ ለአርሶ አደሩ እየቀረበለት እንደሚገኝም ነው የገለጹት።

በተለይ በሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ዙሪያ የለማው የፍራፍሬ ልማት ውጤታማ በመሆኑ በአርሶ አደሩ ዘንድ ከፍተኛ መነሳሳትን መፍጠሩን ነው የገለጹት።


በተሁለደሬ ወረዳ የ012 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሰይድ ፈንታ እንዳሉት ፣ በሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ዙሪያ የለማው የፍራፍሬ ተክል በአጭር ጊዜ ምርት ሲሰጥ መመልከቴ መነሳሳትን ፈጥሮብኛል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅትም በግማሽ ሄክታር ማሳቸው ላይ ከ100 በላይ የተሻሻሉ የሙዝ ችግኞትን መትከላቸውን ገልጸዋል።


የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መሀመድ አደም በበኩላቸው፣ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ መሰረትም ቋሚ የሆኑ ፍራፍሬዎችን እያለሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በጫት ተሸፍኖ የነበረውን ሩብ ሄክታር መሬታቸውን በመመንጠርም ፓፓያና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን እየተከሉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ሉባባ ሰይድ ናቸው።


በደቡብ ወሎ ዞን በመጪው ክረምት በ3 ሺህ 700 ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026

‎ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ተወዳዳሪነቷን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው 

‎ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...

Apr 20, 2026