🔇Unmute
ደሴ ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ወሎ ዞን በኩታገጠም ቋሚ ፍራፍሬን በማልማት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በዞኑ እስከ ሐምሌ 30/2018 የሚዘልቅ 900 ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም እርሻ ፍራፍሬን ለማልማት የሚያስችል የችግኝ ተከላ ዘመቻ ተጀምሯል።
የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዞኑ የፍራፍሬ ችግኝ ተከላውን የሚያካሔደው ተስማሚ ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ባላቸው አምስት ወረዳዎች ነው።
በዚህ የዘመቻ ስራ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ሙዝ፣ ብርቱካንና ሌሎች ቋሚ የፍራፍሬ ችግኞችን የመትከል ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

የችግኝ ተከላው በተሁለደሬ፣ በአምባሰል፣ በቃሉ፣ በወረባቦና በአርጎባ ብሔረሰብ ወረዳዎች እየተከናወነ ነው።
ይህም በዘልማድና በተበታተነ አግባብ የሚካሔዱ የፍራፍሬ ልማት ስራዎችን በማስቀረት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጥ፣ በሽታን የሚከላከልና ምርታማ የፍራፍሬ ችግኝ ለአርሶ አደሩ እየቀረበለት እንደሚገኝም ነው የገለጹት።
በተለይ በሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ዙሪያ የለማው የፍራፍሬ ልማት ውጤታማ በመሆኑ በአርሶ አደሩ ዘንድ ከፍተኛ መነሳሳትን መፍጠሩን ነው የገለጹት።

በተሁለደሬ ወረዳ የ012 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሰይድ ፈንታ እንዳሉት ፣ በሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ዙሪያ የለማው የፍራፍሬ ተክል በአጭር ጊዜ ምርት ሲሰጥ መመልከቴ መነሳሳትን ፈጥሮብኛል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅትም በግማሽ ሄክታር ማሳቸው ላይ ከ100 በላይ የተሻሻሉ የሙዝ ችግኞትን መትከላቸውን ገልጸዋል።

የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መሀመድ አደም በበኩላቸው፣ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ መሰረትም ቋሚ የሆኑ ፍራፍሬዎችን እያለሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በጫት ተሸፍኖ የነበረውን ሩብ ሄክታር መሬታቸውን በመመንጠርም ፓፓያና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን እየተከሉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ሉባባ ሰይድ ናቸው።

በደቡብ ወሎ ዞን በመጪው ክረምት በ3 ሺህ 700 ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026