🔇Unmute
ደሴ ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ወሎ ዞን በኩታገጠም ቋሚ ፍራፍሬን በማልማት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በዞኑ እስከ ሐምሌ 30/2018 የሚዘልቅ 900 ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም እርሻ ፍራፍሬን ለማልማት የሚያስችል የችግኝ ተከላ ዘመቻ ተጀምሯል።
የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ዞኑ የፍራፍሬ ችግኝ ተከላውን የሚያካሔደው ተስማሚ ስነ-ምህዳርና የአየር ንብረት ባላቸው አምስት ወረዳዎች ነው።
በዚህ የዘመቻ ስራ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ሙዝ፣ ብርቱካንና ሌሎች ቋሚ የፍራፍሬ ችግኞችን የመትከል ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

የችግኝ ተከላው በተሁለደሬ፣ በአምባሰል፣ በቃሉ፣ በወረባቦና በአርጎባ ብሔረሰብ ወረዳዎች እየተከናወነ ነው።
ይህም በዘልማድና በተበታተነ አግባብ የሚካሔዱ የፍራፍሬ ልማት ስራዎችን በማስቀረት የአርሶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጥ፣ በሽታን የሚከላከልና ምርታማ የፍራፍሬ ችግኝ ለአርሶ አደሩ እየቀረበለት እንደሚገኝም ነው የገለጹት።
በተለይ በሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ዙሪያ የለማው የፍራፍሬ ልማት ውጤታማ በመሆኑ በአርሶ አደሩ ዘንድ ከፍተኛ መነሳሳትን መፍጠሩን ነው የገለጹት።

በተሁለደሬ ወረዳ የ012 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሰይድ ፈንታ እንዳሉት ፣ በሎጎ ሀይቅ ሪዞርት ዙሪያ የለማው የፍራፍሬ ተክል በአጭር ጊዜ ምርት ሲሰጥ መመልከቴ መነሳሳትን ፈጥሮብኛል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅትም በግማሽ ሄክታር ማሳቸው ላይ ከ100 በላይ የተሻሻሉ የሙዝ ችግኞትን መትከላቸውን ገልጸዋል።

የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መሀመድ አደም በበኩላቸው፣ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ መሰረትም ቋሚ የሆኑ ፍራፍሬዎችን እያለሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በጫት ተሸፍኖ የነበረውን ሩብ ሄክታር መሬታቸውን በመመንጠርም ፓፓያና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞችን እየተከሉ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ሉባባ ሰይድ ናቸው።

በደቡብ ወሎ ዞን በመጪው ክረምት በ3 ሺህ 700 ሄክታር መሬት ላይ የፍራፍሬ ችግኝ ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026