🔇Unmute
ጎንደር፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ አስተዳደር በገጠር ቀበሌዎች ለ100 ሺህ የእርሻ መሬት ባለይዞታዎችዲጂታል ካርታ እና የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ መሬት መምሪያ አስታወቀ፡፡
በከተማው ገጠር ቀበሌዎች ለመሬት ባለይዞታዎች የማረጋገጫ ደብተር ለመስጠት የካዳስተር ሥራ ማስጀመር የሚያስችል የአጋር አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሂዷል፡፡

የመምሪያው ምክትል ሃላፊ አዛናው መልካሙ በመድረኩ እንደገለጹት፤ ዘመናዊ የዲጂታል የመሬት ምዝገባ ስርአት የአርሶ አደሩን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በዘላቂነት የሚፈታ ነው፡፡
በከተማው በታቀፉ 11 የገጠር ቀበሌዎች ለ100 ሺህ የእርሻ መሬት ባለይዞታዎች2ኛ ደረጃ ዲጂታል ካርታና የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ለመስጠት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም 1ሺህ 283 ባለይዞታዎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጸው፣ ማረጋገጫው መሰጠቱ አርሶ አደሩ ህጋዊ የመሬት ባለቤትነቱን በማረጋገጥ መሬቱን ለመንከባከብና ለማልማት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
በተጨማሪም የማረጋገጫ ካርታውን አስይዞ ከአበዳሪ ተቋማት የገንዘብ ብድር እንዲያገኝ ዋስትና እንደሚሰጠው ገልጸው፣ በመሬት ይገባኛል የሚነሱ ግጭቶችን እንደሚያስወግድም አስረድተዋል።
ዲጂታል የይዞታ ማረጋገጫ ካርታና ደብተር የመስጠት ሥራውን በተያዘው የሚያዚያ ወር መጨረሻ በማስጀመር እስከ ቀጣዩ ዓመት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ተወካይ መኮንን ተሾመ በበኩላቸው፤ መሬት ትልቅ ሀብት በመሆኑ መረጃውን በሳይንሳዊ መንገድ ሰንዶ ለሚፈለገው ልማት ማዋል ይገባል ብለዋል።
በጎንደር ከተማ የአንቸው ገጠር ቀበሌ ነዋሪ ሴት አርሶ አደር ተዘሩ አለማየሁ፤ ከዚህ በፊት የተሰጣቸው የመጀመሪያ ደረጃ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ከባንክ ብድር አውጥተው በልማት ስራ ለመሰማራት እንቅፋት እንደሆነባቸው አስታውሰዋል።

አዲሱ ዲጂታል የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ከባንክ ለመበደር ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸው፣ ካርታውን ለማግኘት አስፈላጊውን የባለቤትነት ማስረጃዎች አደራጅቼ እየጠበኩ ነው ብለዋል።
ዲጂታል የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የመሬት ወረራን ለማስቀረት ትልቅ ፋይዳ አለው ያሉት ደግሞ በከተማ አስተዳደሩ የሳቢያ ሳይና ገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር እያዩ አሊ ናቸው፡፡

በምክክር መድረኩ ከገጠር ቀበሌዎች የተውጣጡ አርሶ አደሮች፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026