🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ 22/2018 (ኢዜአ)፡- ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ2 ሚሊየን ለሚልቁ ዜጎች በሀገር ውስጥና በውጭ የሥራ ዕድል መፈጠሩን የኦሮሚያ ክልል የሥራ ዕድል ፈጠራና ክኅሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዋሲሁን ጎልጋ ገለጹ።

ለ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች የሥራ ፈጠራ ሥልጠና መሰጠቱንም ገልጸዋል።
ከእነዚህ መካከልም ፍላጎት ያላቸውን 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ወጣቶች በመለየት በሥራ ዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በኩል የክኅሎት ማሳደጊያ ሥልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ለኢዜአ ተናግረዋል።
ከዞን እስከ ቀበሌ ድረስ ያሉትን ተጨባጭ ሁኔታዎች መሠረት በማድረግ፤ በኢንዱስትሪ፣ በግብርና እና በአገልግሎት ዘርፎች የተለዩ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውንም አስረድተዋል።

ይህ የሥራ ዕድል ፈጠራ ሂደትም በክኅሎት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን በማድረግ ዜጎች በየመስካቸው ውጤታማ እንዲሆኑ መሠራቱን አረጋግጠዋል።
በበጀት ዓመቱ 2 ሚሊየን 720 ሺህ ዜጎችን በማደራጀትና በቅጥር የሥራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱን ጠቁመው፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሀገር ውስጥ ለ2 ሚሊየን 17 ሺህ 208 ዜጎች እንዲሁም 159 ሺህ ዜጎች በውጭ ሀገራት የሥራ ስምሪት እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

ለሥራ ዕድል ተጠቃሚዎቹ ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር አንጻርም፤ 95 ሺህ ሄክታር መሬት ለማምረቻ፣ ከ7 ሺህ በላይ የመሸጫ ሼዶች እንዲሁም ከ23 ቢሊየን ብር በላይ የፋይናንስ አቅርቦት መመቻቸቱን ተናግረዋል።
ወደ ሥራ የገቡ ዜጎች ለሚያመርቷቸው ምርቶች ሰፊ የገበያ ትስስር እንዲፈጠር መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም ውጤታማ የሆኑ 1 ሺህ 800 ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢንቨስትመንት ደረጃ እንዲሸጋገሩ መደረጉን ገልጸዋል።
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡-ሀዋሳ ከተማን የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል በማድረግ ከተማዋ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከተማ እንድትሆን ርብርብ እየተደረ...
Apr 20, 2026