የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ለዓለም አቀፍና ዳያስፖራ ማህበረሰብ የማስገንዝብ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ፍትሐዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ለዓለም አቀፍና ዳያስፖራ ማህበረሰብ የማስገንዝብ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን በዚምባቡዌ፣ ዛምቢያና ሞሪሽየስ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርና የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የኢትዮጵያ ቋሚ ተጠሪ ረሽድ መሀመድ ገለጹ።

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራና ኮሪደር ልማት ውጤታማ ሥራዎች በዲፕሎማሲ መስክ የሀገርን ስምና ገፅታ እያጎሉ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

አምባሳደር ረሽድ መሀመድ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ በኢ-ፍትሐዊ በደል ከታሪካዊ፣ መልክዓምድራዊና ሕጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷ እንድትነጠል መደረጉን አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያ እያስመዘገበችው ካለው ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገትና ካላት የህዝብ ቁጥር አንጻር በባለቤትነት የምታስተዳድረው፣ የወጪና ገቢ ንግዷን የሚያሳልጥላት አስተማማኝ የባሕር በር እንደሚያስፈልጋት አንስተዋል።

በመልክ-ዓምድራዊ አቀማመጥም ከቀይ ባሕር በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኝ እንደመሆኗ ከባሕር በር ባለቤትነት ተነጥላ ልትኖር እንደማይቻላት አስገንዝበዋል።

ከሶስት አስርት ዓመታት በፊት የባሕር በር ባለቤት የነበረች መሆኗም የባሕር በር ባለቤትነቷን ሕጋዊና ምክንያታዊነት እንደሚያጎላው አብራርተዋል።

በዚህም የኢትዮጵያን ታሪካዊ፣ ሕጋዊ፣ መልክዓ-ምድራዊና ፍትሐዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ በተለይም ለዚምባቡዌ፣ ዛምቢያ፣ ሞሪሽየስና ኮሜሳ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የማስገንዘብ ስራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ አድናቆትና ዕውቅና እየተቸረው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በአረንጓዴ አሻራ የተመዘገበውን ስኬት በአፍሪካ ሀገራት ለማስፋት የዲፕሎማቲክ ግሪን ሌጋሲ ፎረም በመመስረት እየተሰራበት መሆኑን ተናግረዋል።

በኤምባሲው አስተባባሪነትም በዚምባቡዌ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተካሄደ እንደሚገኝ አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ከሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክር የዲፕሎማሲ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አምባሳደሩ ጨምረው ገልጸዋል።

ለአብነትም በቅርቡ የኢትዮጵያና ዚምባቡዌ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በማካሄድ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ይበልጥ የሚያጠናክሩ ስምምነቶችን ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ በዛምቢያ በክብር ቆንፅላ እንድትወከል የሚያስችሉ ሥራዎችን በማከናወን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026