🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የተገነቡ ግዙፍ ሰው ተኮር የልማት ፕሮጀክቶች የነዋሪዎችን ሕይወት እያሻሻሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶች፣ ሱቆችናየህጻናት መጫወቻ ፓርኮችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

ከንቲባዋ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፓስተር አካባቢ የተገነባ ባለአምስት ወለል የመኖሪያ ቤት ህንጻን ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች አስረክበዋል።
እንዲሁም በክፍለ ከተማው 40/60 ብርጭቆ ኮንደሚኒየም አካባቢ የተገነቡ ሁለገብ የህዝብ መዝናኛ ፓርክን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ አዲስ አበባ ከስም በዘለለ በተግባር ውብ እና አበባ እየሆነች ትገኛለች ብለዋል።
በከተማዋ የተገነቡ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተመራጭ ከተማ እንድትሆን እንዳስቻሏት ገልጸዋል።

የከተማዋ ልማት ከዜጎች ህይወት መለወጥ እና መዘመን ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው መሆኑን አመላክተዋል።
በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ፣ ምቹ የመኖሪያና የመዝናኛ አማራጭ የሚፈጥሩ እና የቱሪስት መስህብ መሆን የሚችሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ነዋሪዎች የተገነቡትን ውብ የልማት ፕሮጀክቶች በአግባቡ በመጠበቅና በመንከባከብ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የልማት ፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች በበኩላቸው፤ የተገነቡ የመኖሪያ ቤቶች፣ የህፃናት መጫወቻ ፓርኮች ወደ ዘመናዊና ምቹ አኗኗር የሚያሸጋግሩ ናቸው ብለዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026