የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በምርጫው ላይ ያሳየነውን ጠንካራ ተሳትፎ በቀጣይ በጋራ ሀገር ለመገንባት ማዋል አለብን- የጅማ ከተማ ነዋሪዎች

Jun 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤ግንቦት 25/2018(ኢዜአ)፡- በምርጫው ላይ ያሳየነውን ጠንካራ ተሳትፎ በቀጣይ በጋራ ሀገር ለመገንባት ማዋል አለብን ሲሉ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

በጅማ ከተማ ቆጠራ በተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶች እየተለጠፉ ሲሆን፣ ሕዝቡም እየተመለከተ ይገኛል።

በጅማ ከተማ ባሉት 117 የምርጫ ጣቢያዎች ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ድምፃቸውን ሲሰጡ መዋላቸውን የጅማ ከተማ የምርጫ ክልል መግለጹ ይታወቃል።

በከተማዋ ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ሲመለከቱ ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች፤ አጠቃላይ በምርጫ ሂደቱ በትናንትናው እለት ደግሞ ድምፅ ለመስጠት ከማለዳ እስከ ምሽት የነቃ ተሳትፎ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በምርጫው ላይ ያሳየነውን ጠንካራ ተሳትፎ በቀጣይ በጋራ ሀገር ለመገንባት ማዋል አለብን ሲሉ አስተያየት ሰጭዎቹ ተናግረዋል።

ትላንት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድምጻቸውን ሰጥተው፣ በማለዳ ውጤት ለማየት በምርጫ ጣቢያ የተገኙት አቶ አወል አብዱረህማን፤ ሀገርን መውደድ ከሚገለጽባቸው መንገዶች አንዱ በምርጫ መሳተፍ ነው ይላሉ።

ሰላማዊ ምርጫ ተካሂዶ መጠናቀቁ የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸው፤ በምርጫ ያሳየነውን ተሳትፎ በሌሎች የልማት ሥራዎችም መድገም አለብን ብለዋል።

ከዚህም ባለፈ የምርጫ ውጤትን በፀጋ በመቀበል የዴሞክራሲ መሠረትን ማፅናትና የሀገርን ልማት ማፋጠን ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።

ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ በሽር አህመድ በበኩላቸው፣ በምርጫው የነቃ ተሳትፎ አድርገው መምረጣቸውን ገልጸው፤ በቀጣይም ሀገር በምትፈልገው መስክ ሁሉ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ቀደም ሲል በተካሄዱ ምርጫዎች ላይ መሳተፋቸውን ያስታወሱት አቶ በሽር፤ ይህ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በርካታ ዜጎች የተሳተፉበትና ሰላማዊ መሆኑ በእጅጉ እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል።

በመሆኑም በምርጫው የተሳተፉ አካላት ሁሉ ውጤቱን አምኖ በመቀበል የኢትዮጵያን ዕድገትና ሰላም ሊያስቀጥሉ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በምርጫው ድምጿን በመስጠቷ ትልቅ ደስታ እንደተሰማት የገለጸችው ወይዘሮ ዘቢባ ጀማል በበኩሏ፣ ውጤቱን ለማየት በማለዳው በጊንጅ ጉድሩ ቀበሌ ገጠር ቴክኖሎጂ ምርጫ ጣቢያ መገኘቷን ተናግራለች።

በቀጣይም በምርጫው ላይ ያደረጉትን ተሳትፎ ሀገር በምትፈልገው የልማት ሥራዎች ላይ ለመድገም ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በጅማ ከተማ የኢዜአ ሪፖርተር ተዘዋውሮ በተመለከታቸው በጊንጅ ጉድሩ ቀበሌ ገጠር ቴክኖሎጂ ምርጫ ጣቢያ፣ በውኃ ፍሳሽ ምርጫ ጣቢያ እና በሌሎችም ጣቢያዎች የምርጫ ውጤቶች በአሁኑ ሰዓት እየተለጠፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026