የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢንስቲትዩቱ በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን ማስፈልፈል የሚያስችል ዘመናዊ የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል እያስገነባ ነው

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦የጋምቤላ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን ማስፈልፈል የሚያስችል የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል በማስገንባት ላይ መሆኑን አስታወቀ።

ኢንስቲትዩቱ በጋምቤላ ከተማ ከ58 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ እያካሄደ ያለውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ሂደቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ ጎብኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሯ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ማዕከሉ የዶሮ እርባታውን ለማዘመንና ለማስፋት ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል።


በተለይም እንደ ሀገር ጤናማ የአመጋገብ ስርዓትን ለማጠናከር እየተተገበረ ያለውን የሌማት ትሩፋት መርሃግብር ስኬታማ ለማድረግ የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በመሆኑም የግንባታውን ሂደት በማፋጠን ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ለማዕከሉ ግንባታ መፋጠን የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ያደርጋልም ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሯ።

የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሪያል ጂንግ፤ ኢንስቲትዩቱ በምርምር የተሻሻሉ የእንስሳትና የዕጽዋት ዝርያዎችን በማውጣት ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።


ኢንስቲትዩቱ እያስገነባ ያለው የዶሮ ምርምርና ብዜት ማዕከል የተሻሻሉ ዝርያዎች ለአርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች ተደራሽ ለማድረግ ያለም መሆኑንም ተናግረዋል።

በምርምር ኢንስቲትዩቱ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ አብዮት አለማየሁ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ የማዕከሉ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባ በአንድ ዙር 57 ሺህ ጫጩቶችን የማስፈልፈል አቅም አለው።

በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፍ ከ58 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለው ማዕከሉ አሁን ላይ ግንባታው ከ80 ከመቶ በላይ መድረሱን ገልጸዋል።

የማዕከሉን 2ኛ ምዕራፍ ግንባታንም ለማስጀመር የጨረታ ሂደቱ መጠናቀቁንና በቅርቡ ስራው እንደሚጀመር አቶ አብዮት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026