🔇Unmute
ሐረር ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦ በምርጫ ወቅት የታየውን ጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎና አንድነት በልማት ሥራዎች ላይም በመድገም የሀገራቸውን ዕድገት ለማፋጠን ዝግጁ መሆናቸውን በሐረር ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የሐረር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በምርጫው ላይ ያሳዩትን ተሳትፎ በቀጣይ የልማት ስራዎችን በማጠናከር ልማትና እድገትን ማስቀጠል ይጠበቅብናል ብለዋል።
ከነዋሪዎቹ መካከል ወይዘሮ ሙሉነሽ ዋቅቶላ እንዳሉት፤ ምርጫው ህዝቡ በነቂስ በመውጣት ሀገር ወዳድነቱን በግልጽ ያሳየበት ነው።
በምርጫ ያሳየነውን ተሳትፎ በማጎልበት እና የልማት ስራዎችን በማስቀጠል መድገም ይጠበቅብናል ብለዋል።
መምህር ቶማስ ዱባለ ፤ምርጫው የኢትዮጵያንና የሕዝቦቿን ትልቅ ስኬት ያሳየ ነው ሲሉ አክለዋል።
ከዚህም ባለፈ የተጀመሩትን የልማት ስራዎች በማፋጠን ለሀገር ልማት መትጋት ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።
ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ታደሰ በየነ በበኩላቸው፤ ምርጫው የህዝቡ የነቃ ተሳትፎ የታየበት፣ የሀገሪቱን የወደፊት ብሩህ ተስፋ ያሳየና የሚያስደስት እንደነበር አስታውሰዋል።
በቀጣይም በምርጫው ላይ ያደረጉትን ተሳትፎ በልማት ሥራዎች ላይ በመድገም ለልጅ ልጆቻቸው ብሩህ ሀገርን የማሻገር ተግባር እንደሚያከናውኑ ጠቅሰዋል።
ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበትና ሰላማዊ መሆኑ በእጅጉ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ መምህር ደረጀ ተስፋዬ ናቸው።
መምህር ደረጃ ፤ በቀጣይም ሀገራዊም ሆነ ክልላዊ የልማት ስራዎች ላይ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026