🔇Unmute
ሐረር ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦ በምርጫ ወቅት የታየውን ጠንካራ የሕዝብ ተሳትፎና አንድነት በልማት ሥራዎች ላይም በመድገም የሀገራቸውን ዕድገት ለማፋጠን ዝግጁ መሆናቸውን በሐረር ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የሐረር ከተማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በምርጫው ላይ ያሳዩትን ተሳትፎ በቀጣይ የልማት ስራዎችን በማጠናከር ልማትና እድገትን ማስቀጠል ይጠበቅብናል ብለዋል።
ከነዋሪዎቹ መካከል ወይዘሮ ሙሉነሽ ዋቅቶላ እንዳሉት፤ ምርጫው ህዝቡ በነቂስ በመውጣት ሀገር ወዳድነቱን በግልጽ ያሳየበት ነው።
በምርጫ ያሳየነውን ተሳትፎ በማጎልበት እና የልማት ስራዎችን በማስቀጠል መድገም ይጠበቅብናል ብለዋል።
መምህር ቶማስ ዱባለ ፤ምርጫው የኢትዮጵያንና የሕዝቦቿን ትልቅ ስኬት ያሳየ ነው ሲሉ አክለዋል።
ከዚህም ባለፈ የተጀመሩትን የልማት ስራዎች በማፋጠን ለሀገር ልማት መትጋት ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።
ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ታደሰ በየነ በበኩላቸው፤ ምርጫው የህዝቡ የነቃ ተሳትፎ የታየበት፣ የሀገሪቱን የወደፊት ብሩህ ተስፋ ያሳየና የሚያስደስት እንደነበር አስታውሰዋል።
በቀጣይም በምርጫው ላይ ያደረጉትን ተሳትፎ በልማት ሥራዎች ላይ በመድገም ለልጅ ልጆቻቸው ብሩህ ሀገርን የማሻገር ተግባር እንደሚያከናውኑ ጠቅሰዋል።
ምርጫው በርካታ ዜጎች የተሳተፉበትና ሰላማዊ መሆኑ በእጅጉ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ መምህር ደረጀ ተስፋዬ ናቸው።
መምህር ደረጃ ፤ በቀጣይም ሀገራዊም ሆነ ክልላዊ የልማት ስራዎች ላይ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026