የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጠናከር በትኩረት መስራቷን ትቀጥላለች

Jun 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማሳደግ የምታከናውናቸውን ተግባራት አጠናክራ እንደምትቀጥል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ።

የኢትዮጵያን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለኢዜአ እንዳሉት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል ልማት በትኩረት እየሰራች ትገኛለች።

ባለፉት ዓመታት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ ሶስት ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደስራ ማስገባት መቻሉን ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት በስፋት መስራቷ በዘርፉ ተጠቃሽ ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ እንድትሆን ያስቻላት መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የምታመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ከታዳሽና ንፁህ ኃይል የሚገኝ መሆኑንም አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ተቋም ውስጥ በግንባር ቀደምነት እየሰራች መሆኗን አንስተው፤ ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ለማጎልበት የምታከናውነውን ተግባር አጠናክራ መቀጠሏንም ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ ኃይል ከምታቀርብላቸው ከጅቡቲ፣ ሱዳንና ኬንያ በተጨማሪ ወደ ታንዛኒያ የኃይል ሽያጭ ሙከራ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ከሌሎች ሀገራት ጋርም በኃይል ለመተሳሰር ጥናት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ለውጭ ሀገራት የምታቀርበው ከምታመነጨው ኃይል አስር በመቶ ያነሰ እንደሆነ በመግለጽ፤ የሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት የምታቀርበውን ኃይል በማቀናጀት በታዳሽ ኃይል ቀዳሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ግዙፍ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

16 የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮጀክቶችም በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ተቋሙ የኢትዮጵያን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026