🔇Unmute
ጋምቤላ፤ ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአረንጓዴ ዐሻራ እና የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብሮች የፈጠሩትን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስኬታማ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጋምቤላ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አንድሮው ቱት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ሐባብና ብርቱካንን ጨምሮ ሌሎች አትክልትና ፍራፍሬዎች በአርሶ አደሮችና ባለሃብቶች በስፋት እየተመረቱ ነው።
በተለይም በጎደሬና በመንጌሽ ወረዳዎች አቮካዶና ሙዝን ጨምሮ ሌሎች የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ወደ አዲስ አበባና ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለገበያ በስፋት እየቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል።
በዘንድሮው ክረምትም ከአረንጓዴ ዐሻራ ልማቱ ጋር በማቀናጀት አቮካዶን ጨምሮ ከ8 ሚሊየን በላይ የፍራፍሬና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

የጎደሬ ወረዳ ጌለሻ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሉቃስ ጎርሾ፤ ሙዝ፣ አቮካዶና ሌሎችንም የሰብል እንዲሁም አትክልትና ፍራፍሬዎች በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ባለፉት ዓመታት በሙዝ ልማት በስፋት በመሰማራት ተጠቃሚ መሆኑን የገለጸው ደግሞ የዚሁ ቀበሌ ነዋር ወጣት ሮቤል ሮኬት ነው።

በአሁኑ ወቅት በሰባት ሔክታር ላይ ሙዝ በማልማት ምርቱን በአዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች በመሸጥ ተጠቃሚ መሆኑን ነው ያረጋገጠው።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026