የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን የሚተኩ እና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶች በስፋትና በጥራት እንዲመረቱ አስችሏል

Jun 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ኮምቦልቻ ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ምርትን በመተካትና ለውጭ ምንዛሬ ግኝት የሚሆኑ ምርቶችን በጥራትና በስፋት በማምረት ረገድ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ።

«ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው የአማራ ክልል ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በኮምቦልቻ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ ንቅናቄው ባለፉት ዓመታት የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማሳደግና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ከፍተኛ ሚና አበርክቷል።

ሚኒስትሩ አክለውም፣ በንቅናቄው አማካኝነት ኢንዱስትሪዎችን መደገፍ፣ መሠረተ ልማቶችን ማሟላት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና በተግዳሮቶች ላይ መፍትሔ መስጠት መቻሉን ገልጸው፤ በእነዚህም ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል።

በተጨማሪም ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን ከመተካትና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶችን በጥራትና በብዛት ከማምረት ባሻገር፣ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በአማራ ክልልም ንቅናቄው በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩና አዳዲስ ባለሃብቶችም በኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።


የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፤ በክልሉ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተቻለ ሲሆን፣ ይህም የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።

ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን በመተካትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረት ረገድ ካስገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር፣ ማኅበረሰቡ በሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀምና በራሱ ምርት የመኩራት ባሕል እንዲያዳብር ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ተናግረዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይም ዘርፉን የመደገፍ፣ የማዘመንና የማስፋት ሥራዎችን በማጠናከር ይበልጥ ተጠቃሚ ለመሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም የክልሉ መንግሥት ለዚህ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው፤ በንቅናቄው አማካኝነት ባለፉት አራት ዓመታት 496 የሚሆኑ አዳዲስና ነባር ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።


ከዚህ በተጨማሪም በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፉ ከ125 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።

አቶ እንድሪስ አክለውም፤ በንቅናቄው አማካኝነት ከባለሀብቶች ጋር በቅርብ በመሥራት ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የብድር አቅርቦት እንዲያገኙ፣ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉላቸው እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያገኙ መቻሉን ገልጸዋል።

በመርሐግብሩ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026