የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን የሚተኩ እና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶች በስፋትና በጥራት እንዲመረቱ አስችሏል

Jun 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ኮምቦልቻ ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ):- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ ምርትን በመተካትና ለውጭ ምንዛሬ ግኝት የሚሆኑ ምርቶችን በጥራትና በስፋት በማምረት ረገድ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለፁ።

«ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት» በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው የአማራ ክልል ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በኮምቦልቻ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንደገለጹት፤ ንቅናቄው ባለፉት ዓመታት የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማሳደግና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ከፍተኛ ሚና አበርክቷል።

ሚኒስትሩ አክለውም፣ በንቅናቄው አማካኝነት ኢንዱስትሪዎችን መደገፍ፣ መሠረተ ልማቶችን ማሟላት፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና በተግዳሮቶች ላይ መፍትሔ መስጠት መቻሉን ገልጸው፤ በእነዚህም ዘርፎች ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን አስረድተዋል።

በተጨማሪም ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን ከመተካትና የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶችን በጥራትና በብዛት ከማምረት ባሻገር፣ ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቻሉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በአማራ ክልልም ንቅናቄው በርካታ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩና አዳዲስ ባለሃብቶችም በኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።


የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፤ በክልሉ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተቻለ ሲሆን፣ ይህም የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።

ንቅናቄው የገቢ ምርቶችን በመተካትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረት ረገድ ካስገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር፣ ማኅበረሰቡ በሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀምና በራሱ ምርት የመኩራት ባሕል እንዲያዳብር ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ተናግረዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይም ዘርፉን የመደገፍ፣ የማዘመንና የማስፋት ሥራዎችን በማጠናከር ይበልጥ ተጠቃሚ ለመሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም የክልሉ መንግሥት ለዚህ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ በበኩላቸው፤ በንቅናቄው አማካኝነት ባለፉት አራት ዓመታት 496 የሚሆኑ አዳዲስና ነባር ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።


ከዚህ በተጨማሪም በኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፉ ከ125 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።

አቶ እንድሪስ አክለውም፤ በንቅናቄው አማካኝነት ከባለሀብቶች ጋር በቅርብ በመሥራት ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የብድር አቅርቦት እንዲያገኙ፣ መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉላቸው እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያገኙ መቻሉን ገልጸዋል።

በመርሐግብሩ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026