🔇Unmute
ሐረር፤ ሰኔ 2/2018 (ኢዜአ) ፡-በሐረሪ ክልል ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር የተሳሰሩ አዳዲስ የገጠር መንገዶችን የመገንባት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በሀገሪቱ ከተሞች የተጀመረውና ውጤታማነቱ የተመሰከረለት የኮሪደር ልማት ንቅናቄ፣ በአሁኑ ወቅት ወደ ገጠር አካባቢዎች በመስፋፋት ላይ ይገኛል።
የሐረሪ ክልልም ይህንን ሀገራዊ ራዕይ ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም የከተማና የገጠር ትስስርን ለማጠናከር በትኩረት እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኢንጅነር ፈቲህ ተውፊቅ እንዳሉት፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በገጠር የመንገድ ተደራሽነትን ለማጎልበት መጠነ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።
የጠጠር መንገድ ግንባታ ሥራዎቹም ለአርሶ አደሩ በበጋና በክረምት ምርቱን ወደ ገበያ እንዲያቀርብ በማድረግና ሌሎች አገልግሎት በመስጠት ተጠቃሚነትን እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።

ዘንድሮም በተለያዩ ፕሮግራሞች የገጠር መንገድ ተደራሽነትን በማጎልበት የከተማና ገጠር ትስስርን የማጠናከር እና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በክልሉ ሶስት ወረዳዎች በመደበኛ በጀትና በገጠር መንገድ ትስስር ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም 77 ኪሎ ሜትር አዳዲስ የገጠር መንገድ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በካፒታል ፕሮጀክት 54 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን አዳዲስ የገጠር መንገዶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ ቀሪው 23 ኪሎ ሜትር ግንባታ ደግሞ በገጠር መንገድ ትስስር ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም አማካኝነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር በማስተሳሰር እየተካሄደ ያለው አዳዲስ የገጠር ጠጠር መንገዶች ግንባታን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አዳዲስ የጠጠር መንገድ ግንባታዎቹ በህዝቡ ዘንድ ሲነሱ የነበሩ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ከመሆናቸው ባለፈ ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር የተሳሳሩ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የመንገዶቹ መገንባትም ቀበሌዎችን እርስ በእርስና ከከተማው ጋር የሚያገናኝ መሆኑን ጠቁመው በዚህም በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋለውን ችግር ከመሠረቱ የሚቀርፍ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በከተማው ውስጥ አዳዲስ የአስፋልትና የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ፣ የጥገና፣ ደረጃዎችን የማሻሻልና ሌሎች ስራዎችን የማከናወን ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አክለዋል።
በሐረሪ ክልል በሁለተኛው ዙር ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ፕሮጀክት 250 ቤቶች የመገንባት ስራ በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026