🔇Unmute
ሐረር፤ ሰኔ 2/2018 (ኢዜአ) ፡-በሐረሪ ክልል ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር የተሳሰሩ አዳዲስ የገጠር መንገዶችን የመገንባት ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በሀገሪቱ ከተሞች የተጀመረውና ውጤታማነቱ የተመሰከረለት የኮሪደር ልማት ንቅናቄ፣ በአሁኑ ወቅት ወደ ገጠር አካባቢዎች በመስፋፋት ላይ ይገኛል።
የሐረሪ ክልልም ይህንን ሀገራዊ ራዕይ ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም የከተማና የገጠር ትስስርን ለማጠናከር በትኩረት እየሰራ መሆኑ ይታወቃል።
የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኢንጅነር ፈቲህ ተውፊቅ እንዳሉት፤ በክልሉ ባለፉት ዓመታት በገጠር የመንገድ ተደራሽነትን ለማጎልበት መጠነ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።
የጠጠር መንገድ ግንባታ ሥራዎቹም ለአርሶ አደሩ በበጋና በክረምት ምርቱን ወደ ገበያ እንዲያቀርብ በማድረግና ሌሎች አገልግሎት በመስጠት ተጠቃሚነትን እያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።

ዘንድሮም በተለያዩ ፕሮግራሞች የገጠር መንገድ ተደራሽነትን በማጎልበት የከተማና ገጠር ትስስርን የማጠናከር እና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በክልሉ ሶስት ወረዳዎች በመደበኛ በጀትና በገጠር መንገድ ትስስር ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም 77 ኪሎ ሜትር አዳዲስ የገጠር መንገድ ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በካፒታል ፕሮጀክት 54 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን አዳዲስ የገጠር መንገዶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ ቀሪው 23 ኪሎ ሜትር ግንባታ ደግሞ በገጠር መንገድ ትስስር ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም አማካኝነት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር በማስተሳሰር እየተካሄደ ያለው አዳዲስ የገጠር ጠጠር መንገዶች ግንባታን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አዳዲስ የጠጠር መንገድ ግንባታዎቹ በህዝቡ ዘንድ ሲነሱ የነበሩ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ ከመሆናቸው ባለፈ ከገጠር ኮሪደር ልማት ጋር የተሳሳሩ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የመንገዶቹ መገንባትም ቀበሌዎችን እርስ በእርስና ከከተማው ጋር የሚያገናኝ መሆኑን ጠቁመው በዚህም በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋለውን ችግር ከመሠረቱ የሚቀርፍ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በከተማው ውስጥ አዳዲስ የአስፋልትና የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ፣ የጥገና፣ ደረጃዎችን የማሻሻልና ሌሎች ስራዎችን የማከናወን ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አክለዋል።
በሐረሪ ክልል በሁለተኛው ዙር ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ፕሮጀክት 250 ቤቶች የመገንባት ስራ በመካሄድ ላይ መሆኑ ይታወቃል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026