የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ወልድያ የሰላም፣የመረጋጋትና የፈጣን ልማት ተምሳሌት ከተማ ሆናለች-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2/2018 (ኢዜአ)፦የወልድያ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፣ ከተማዋ የሰላምና የኢኮኖሚ ልማት ተምሳሌት እንድትሆን ማስቻሉን የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) ገለጹ።

በጦርነትና በተለያዩ የሰላም እጥረት ፈተናዎች የጉዳት ሰለባ ሆና የቆየችው ወልድያ ከተማ፣ በአሁኑ ወቅት እያስመዘገበችው ባለው ፈጣን የኮሪደር ልማትና ዘመናዊነት የክልሉ ከተሞች የብልጽግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷንም አንስተዋል።

የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወልድያ ከተማ ሰፊ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በምሽት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


ወልድያ ያስመዘገበችው ለውጥ ለሌሎች ከተሞች ድንቅ ተሞክሮ እንደሚሆን ተናግረዋል።

​የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን( ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በሰሜኑ ጦርነትና በፅንፈኛ ቡድኖች ግጭት ምክንያት ጎስቁላ የነበረችው ወልድያ፣ ዛሬ ላይ የዘመናዊ ከተሜነት መገለጫ ሆናለች።

በወልድያ ከተማ ስንንቀሳቀስ የኮሪደር ልማት ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር ስራዎች ጭምር መሰራታቸውን ተመልክተናል ብለዋል።


ከተማዋና ነዋሪዎቿ ፈተናዎችን በፅናት መሻገራቸውን ጠቅሰው፤ የኮሪደር ልማቱ ህጻናት ከወላጆቻቸው ጋር በምሽት ጭምር በፋውንቴኖች አካባቢ ሲጫወቱ፣ ነዋሪዎችም ፊታቸው ላይ ደስታ እየተነበበ ሲዝናኑ መመልከት ትልቅ ትርጉም አለው ነው ያሉት።


ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም፣ ይህ ለውጥ የመጣው በብልፅግና መንግስት የመደመር እሳቤ ከተሞች ሳይፈርሱና ታሪካዊ ይዞታቸውን ሳይለቁ፣ ዘመናዊና ጽዱ እንዲሆኑ በተነደፈው መርሃ-ግብር መሆኑን ገልጸዋል።

ሀሳቡን በተግባር ለተረጎሙት የከተማዋ አመራሮች፣ ባለሀብቶች፣ ህብረተሰቡና አካባቢውን በፅናት ለጠበቁት የሀገር መከላከያ ሰራዊትና የጸጥታ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

ጠላቶች ስራ አጥነትንና የኢኮኖሚ ችግርን እንደ ማገዶ ለመጠቀም ቢሞክሩም፣ የክልሉ መንግስት በ2018 በጀት ዓመት ተግባራዊ ማድረግ የጀመረው የ25 ዓመት የአሻጋሪ እድገትና ዘላቂ ልማት እቅድ ውጤት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኢኮኖሚ እድገት፣ የስራ እድል ፈጠራና የኢንተርፕራይዞች ልማት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው ብለዋል።


የወልድያ ከተማ ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፥ የከተማዋ አመራር በጦርነት የቆሰለችውን ከተማ ለመቀየር በትልቅ ቁጭት መነሳቱን ገልጸዋል።

በከተማዋ አጠቃላይ 6 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ የተከናወነ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ​የአረንጓዴ ስፍራዎች፣ፓርኮችና የፓርኪንግ ቦታዎች፣ ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠሪያ የሆኑ ዘመናዊ ሼዶች፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን ያካተተ ነው ብለዋል።

አሁን ከተማዋን ውብ፣ ጽዱና ለነዋሪዎቿ የተመቸች ብቻ ሳይሆን፣ ጎብኝዎች ውለው የሚያድሩባት የሰሜን ኢትዮጵያ የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ በተሳካ ሁኔታ መቀጠሉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026