የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ወልድያ የሰላም፣የመረጋጋትና የፈጣን ልማት ተምሳሌት ከተማ ሆናለች-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2/2018 (ኢዜአ)፦የወልድያ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፣ ከተማዋ የሰላምና የኢኮኖሚ ልማት ተምሳሌት እንድትሆን ማስቻሉን የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) ገለጹ።

በጦርነትና በተለያዩ የሰላም እጥረት ፈተናዎች የጉዳት ሰለባ ሆና የቆየችው ወልድያ ከተማ፣ በአሁኑ ወቅት እያስመዘገበችው ባለው ፈጣን የኮሪደር ልማትና ዘመናዊነት የክልሉ ከተሞች የብልጽግና ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷንም አንስተዋል።

የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወልድያ ከተማ ሰፊ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በምሽት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


ወልድያ ያስመዘገበችው ለውጥ ለሌሎች ከተሞች ድንቅ ተሞክሮ እንደሚሆን ተናግረዋል።

​የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን( ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በሰሜኑ ጦርነትና በፅንፈኛ ቡድኖች ግጭት ምክንያት ጎስቁላ የነበረችው ወልድያ፣ ዛሬ ላይ የዘመናዊ ከተሜነት መገለጫ ሆናለች።

በወልድያ ከተማ ስንንቀሳቀስ የኮሪደር ልማት ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር ስራዎች ጭምር መሰራታቸውን ተመልክተናል ብለዋል።


ከተማዋና ነዋሪዎቿ ፈተናዎችን በፅናት መሻገራቸውን ጠቅሰው፤ የኮሪደር ልማቱ ህጻናት ከወላጆቻቸው ጋር በምሽት ጭምር በፋውንቴኖች አካባቢ ሲጫወቱ፣ ነዋሪዎችም ፊታቸው ላይ ደስታ እየተነበበ ሲዝናኑ መመልከት ትልቅ ትርጉም አለው ነው ያሉት።


ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም፣ ይህ ለውጥ የመጣው በብልፅግና መንግስት የመደመር እሳቤ ከተሞች ሳይፈርሱና ታሪካዊ ይዞታቸውን ሳይለቁ፣ ዘመናዊና ጽዱ እንዲሆኑ በተነደፈው መርሃ-ግብር መሆኑን ገልጸዋል።

ሀሳቡን በተግባር ለተረጎሙት የከተማዋ አመራሮች፣ ባለሀብቶች፣ ህብረተሰቡና አካባቢውን በፅናት ለጠበቁት የሀገር መከላከያ ሰራዊትና የጸጥታ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

ጠላቶች ስራ አጥነትንና የኢኮኖሚ ችግርን እንደ ማገዶ ለመጠቀም ቢሞክሩም፣ የክልሉ መንግስት በ2018 በጀት ዓመት ተግባራዊ ማድረግ የጀመረው የ25 ዓመት የአሻጋሪ እድገትና ዘላቂ ልማት እቅድ ውጤት እያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኢኮኖሚ እድገት፣ የስራ እድል ፈጠራና የኢንተርፕራይዞች ልማት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው ብለዋል።


የወልድያ ከተማ ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፥ የከተማዋ አመራር በጦርነት የቆሰለችውን ከተማ ለመቀየር በትልቅ ቁጭት መነሳቱን ገልጸዋል።

በከተማዋ አጠቃላይ 6 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ የተከናወነ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ​የአረንጓዴ ስፍራዎች፣ፓርኮችና የፓርኪንግ ቦታዎች፣ ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠሪያ የሆኑ ዘመናዊ ሼዶች፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን ያካተተ ነው ብለዋል።

አሁን ከተማዋን ውብ፣ ጽዱና ለነዋሪዎቿ የተመቸች ብቻ ሳይሆን፣ ጎብኝዎች ውለው የሚያድሩባት የሰሜን ኢትዮጵያ የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ በተሳካ ሁኔታ መቀጠሉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026