የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጥና በወጣቶች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ውጤት አምጥቷል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ሰኔ 5/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጥና በወጣቶች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ውጤት ማምጣቱን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ገለፀ፡፡

የሲዳማ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ በራሳ ለኢዜአ እንደተናገሩት የአምስት ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ በክልሉ በመንግስታዊ አገልግሎትና በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ውጤት አምጥቷል።

በክልሉ ሰልጥነው ምስክር ወረቀት ካገኙት ውስጥ የመንግስት ሠራተኞች፣ በተለያዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ያሉ ወጣቶች እንዲሁም ተማሪዎች እንደሚገኙበት ገልጸዋል።

በክልሉ ብዙ የመንግስት ሠራተኞች የዲጂታል ክህሎት ባለቤት መሆናቸው ውጤታማ መንግስታዊ አገልግሎት ለመስጠት ጉልህ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል።

ሥልጠናውን የወሰዱ ወጣቶችም በአሁን ወቅት በዲጂታል ኢኮኖሚ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን በመጠቀም ገቢ የማግኘት ዕድላቸውን ማስፋታቸውንም አክለዋል።


በክልሉ ሥልጠናውን ወስደው ካጠናቀቁ ዜጎች መካከል በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ ወይዘሮ ሙሉወርቅ መኳንት አንዷ ናቸው።

በተለያዩ ኮርሶች የሚሰጡ የኮደርስ ስልጠናዎችን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት እንደወሰዱ ገልጸው በሥልጠናው የቴክኖሎጂ እውቀታቸው ያሳደጉና ለስራቸው አጋዥ የሆኑ ብዙ ክህሎቶችን ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

ዲጂታል አሰራር በተለይ ለጤናው ዘርፍ አገልግሎት ቅልጥፍናና ተደራሽነት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረው፣ ስልጠናው በስራቸው አገልግሎቶችን በተሻለ መንገድ ለመስጠት አስችሎኛል ብለዋል።


ወጣት አብርሀም ጥላሁን በበኩሉ በሀዋሳ ከተማ በግል ድርጅት ውስጥ በመተግበሪያ አልሚነት ተቀጥሮ እየሰራ መሆኑን ገልጾ፣ የኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና ሁሉንም ኮርሶች መውሰዱን ተናግሯል፡፡

ድርጅቱ የተለያዩ መተግበሪያዎችን አልምቶ ለተጠቃሚዎች የማቅረብ እንዲሁም የኔትወርክ ዝርጋታ እና የኦንላይን ገበያ ላይ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጿል።

በተቋሙ የሚለሙ መተግበሪያዎች ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር አብረው እንዲሄዱ ለማድረግ ብሎም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታችን እንዲጨምር የኮደርስ ሥልጠና መውሰዴ ጠቅሞኛል ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026