የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጥና በወጣቶች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ውጤት አምጥቷል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ሰኔ 5/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጥና በወጣቶች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ውጤት ማምጣቱን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ገለፀ፡፡

የሲዳማ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተፈራ በራሳ ለኢዜአ እንደተናገሩት የአምስት ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ በክልሉ በመንግስታዊ አገልግሎትና በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ውጤት አምጥቷል።

በክልሉ ሰልጥነው ምስክር ወረቀት ካገኙት ውስጥ የመንግስት ሠራተኞች፣ በተለያዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ያሉ ወጣቶች እንዲሁም ተማሪዎች እንደሚገኙበት ገልጸዋል።

በክልሉ ብዙ የመንግስት ሠራተኞች የዲጂታል ክህሎት ባለቤት መሆናቸው ውጤታማ መንግስታዊ አገልግሎት ለመስጠት ጉልህ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል።

ሥልጠናውን የወሰዱ ወጣቶችም በአሁን ወቅት በዲጂታል ኢኮኖሚ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን በመጠቀም ገቢ የማግኘት ዕድላቸውን ማስፋታቸውንም አክለዋል።


በክልሉ ሥልጠናውን ወስደው ካጠናቀቁ ዜጎች መካከል በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ ወይዘሮ ሙሉወርቅ መኳንት አንዷ ናቸው።

በተለያዩ ኮርሶች የሚሰጡ የኮደርስ ስልጠናዎችን በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት እንደወሰዱ ገልጸው በሥልጠናው የቴክኖሎጂ እውቀታቸው ያሳደጉና ለስራቸው አጋዥ የሆኑ ብዙ ክህሎቶችን ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

ዲጂታል አሰራር በተለይ ለጤናው ዘርፍ አገልግሎት ቅልጥፍናና ተደራሽነት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረው፣ ስልጠናው በስራቸው አገልግሎቶችን በተሻለ መንገድ ለመስጠት አስችሎኛል ብለዋል።


ወጣት አብርሀም ጥላሁን በበኩሉ በሀዋሳ ከተማ በግል ድርጅት ውስጥ በመተግበሪያ አልሚነት ተቀጥሮ እየሰራ መሆኑን ገልጾ፣ የኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና ሁሉንም ኮርሶች መውሰዱን ተናግሯል፡፡

ድርጅቱ የተለያዩ መተግበሪያዎችን አልምቶ ለተጠቃሚዎች የማቅረብ እንዲሁም የኔትወርክ ዝርጋታ እና የኦንላይን ገበያ ላይ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጿል።

በተቋሙ የሚለሙ መተግበሪያዎች ከሰው ሰራሽ አስተውሎት ጋር አብረው እንዲሄዱ ለማድረግ ብሎም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታችን እንዲጨምር የኮደርስ ሥልጠና መውሰዴ ጠቅሞኛል ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026

በዞኑ የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ወደ ስራ ለማሰገባት አስችሏል

አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...

Jul 24, 2026

 በዞኑ እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...

Jul 23, 2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 16, 2026