የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሀዋሳ ሀይቅ ዳር ልማት ፕሮጀክት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን አሰናስሎ ሊገነባ ነው

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የሀዋሳ የሀይቅ ዳር ልማት ፕሮጀክት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን አሰናስሎ ሊገነባ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

በ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የሚከናወነው የሀይቅ ዳር ልማት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ፍቅር ሀይቅ ዳርቻ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የሀዋሳ የሀይቅ ዳር ልማት ፕሮጀክት በመጀመሪያው ምዕራፍ የፍቅር ሀይቅ፣ አሞራ ገደል፣ አሳ ገበያን የያዘ ሲሆን በዛሬው እለት በይፋ ስራ የሚጀምረው ሀይቅ ዳርቻ ልማት ትልቁ የመዝናኛ ማዕከል መሆኑ ተገልጿል።

በፕሮጀክቱ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው በሀዋሳ ከተማ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ ኢንጅነር ቸርነት ፍላቴ፤ የፕሮጀክቱ ግንባታ የተለያዩ መገልገያዎችን ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል።

የፕሮጀክቱ ግንባታ ሬስቶራንቶች፣ ሱቆች፣ የመመልከቻ ማማዎች፣ የዓሳ ማስገሪያ፣ የህዝብ መሰብሰቢያ፣ ሰገነቶች፣ የጎርፍ ውሀ ማጣሪያ፣ የሀይቅ ዳርቻ የብስክሌና የእግረኛ መንገዶች እንዲሁም ሌሎችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።

የሀይቅዳርቻ ልማት ፕሮጀክቱም በስድስት ወራት በጥራት ተገንብቶ ለአገልገሎት የሚበቃ ሲሆን በግንባታው ከ1 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም አንስተዋል።

ከጥቁር ውሀ እስከ ታቦር ተራራ 12 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን የሀይቅ ዳርቻ ልማት የሚከናወን መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ፣ ሌሎች የክልሉና የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ ባለሃብቶች፣ ባለሙያዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026