🔇Unmute
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የሀዋሳ የሀይቅ ዳር ልማት ፕሮጀክት የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን አሰናስሎ ሊገነባ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
በ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የሚከናወነው የሀይቅ ዳር ልማት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ፍቅር ሀይቅ ዳርቻ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የሀዋሳ የሀይቅ ዳር ልማት ፕሮጀክት በመጀመሪያው ምዕራፍ የፍቅር ሀይቅ፣ አሞራ ገደል፣ አሳ ገበያን የያዘ ሲሆን በዛሬው እለት በይፋ ስራ የሚጀምረው ሀይቅ ዳርቻ ልማት ትልቁ የመዝናኛ ማዕከል መሆኑ ተገልጿል።

በፕሮጀክቱ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው በሀዋሳ ከተማ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ ኢንጅነር ቸርነት ፍላቴ፤ የፕሮጀክቱ ግንባታ የተለያዩ መገልገያዎችን ያካተተ መሆኑን አስረድተዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ሬስቶራንቶች፣ ሱቆች፣ የመመልከቻ ማማዎች፣ የዓሳ ማስገሪያ፣ የህዝብ መሰብሰቢያ፣ ሰገነቶች፣ የጎርፍ ውሀ ማጣሪያ፣ የሀይቅ ዳርቻ የብስክሌና የእግረኛ መንገዶች እንዲሁም ሌሎችን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።
የሀይቅዳርቻ ልማት ፕሮጀክቱም በስድስት ወራት በጥራት ተገንብቶ ለአገልገሎት የሚበቃ ሲሆን በግንባታው ከ1 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም አንስተዋል።
ከጥቁር ውሀ እስከ ታቦር ተራራ 12 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን የሀይቅ ዳርቻ ልማት የሚከናወን መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ፣ ሌሎች የክልሉና የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ ባለሃብቶች፣ ባለሙያዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026
አምቦ፤ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሰፈነው ስላም የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እን...
Jul 24, 2026
ጎንደር፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በማእከላዊ ጎንደር ዞን የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የዞኑ ከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...
Jul 16, 2026