የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ምክር ቤቱ ሦስት አዋጆችን አፀደቀ

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስና የኢትዮጵያ ካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጆችን አፀደቀ።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 29ኛ መደበኛ ስብሰባ ከአዋጅ ማፅደቅ በተጨማሪ የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት እቅድ ላይ በዝርዝር ተወያይቷል።


የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ረቂቅ አዋጆቹን የተመለከተ ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

ሰብሳቢው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ በታክስ ከፋዩና በታክስ ሰብሳቢው የሚነሱ አለመግባባቶችን ለመፍታት፣ ተጠያቂነትና ፍትሐዊነትን ለማስፈን ብሎም ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

አዋጁ ገለልተኛ አስማሚ እንዲመደብ በማድረግ አለመግባባቶችን በአማራጭ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል በመሆኑ ምክር ቤቱ እንዲያፀድቀው ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ የዕድገት ጉዞና የለውጥ ፕሮግራሞች እንዲሁም የፖሊስ አወጣጡን በመረጃ ላይ የተደገፈ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ዘመናዊ ጠንካራና ህጋዊ መሰረት ያለውና ዓለም አቀፍ ስርዓትን የተከተለ የስታቲስቲክስ ማዕቀፍ እንዲኖር የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።


የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ የኢትዮጵያ ካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ እያደገ የመጣውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ወደ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማሻገር፣ የአረንጓዴ ኢንቨስትመንትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ የሚረዳ ነው ብለዋል።

ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴው የቀረቡ የውሳኔ ሃሳቦችን በመመርመር ሦስቱን ረቂቅ አዋጆች አጽድቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ምክር ቤቱ ሦስት አዋጆችን አፀደቀ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስና የኢትዮጵያ ካርበን ገበያ ...

Jul 1, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተቋቋሙ የግብይት ማዕከላት የተረጋጋ የገበያ ስርዓት ፈጥረዋል

ሆሳዕና ፤ሰኔ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተቋቋሙ የግብይት ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተረጋጋ የገበያ ስርዓት እየ...

Jun 30, 2026

በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ሊጠናከር ይገባል 

ጋምቤላ፤ ሰኔ 18/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለተያዘው ግብ መሳካት፣ የባለድ...

Jun 26, 2026

አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ሜትር ከፍታ ላይ እየተገነባ ይገኛል

‎አዲስ አበባ፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ከአዲስ አበባ 40 ኪ.ሜ ርቀት ላይ፣ ከባሕር ጠለል በላይ በ1,910 ...

Jun 16, 2026