🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ፣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስና የኢትዮጵያ ካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጆችን አፀደቀ።
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 29ኛ መደበኛ ስብሰባ ከአዋጅ ማፅደቅ በተጨማሪ የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት እቅድ ላይ በዝርዝር ተወያይቷል።

የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ ረቂቅ አዋጆቹን የተመለከተ ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
ሰብሳቢው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ በታክስ ከፋዩና በታክስ ሰብሳቢው የሚነሱ አለመግባባቶችን ለመፍታት፣ ተጠያቂነትና ፍትሐዊነትን ለማስፈን ብሎም ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
አዋጁ ገለልተኛ አስማሚ እንዲመደብ በማድረግ አለመግባባቶችን በአማራጭ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል በመሆኑ ምክር ቤቱ እንዲያፀድቀው ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ የዕድገት ጉዞና የለውጥ ፕሮግራሞች እንዲሁም የፖሊስ አወጣጡን በመረጃ ላይ የተደገፈ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ዘመናዊ ጠንካራና ህጋዊ መሰረት ያለውና ዓለም አቀፍ ስርዓትን የተከተለ የስታቲስቲክስ ማዕቀፍ እንዲኖር የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ የኢትዮጵያ ካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ እያደገ የመጣውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ወደ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማሻገር፣ የአረንጓዴ ኢንቨስትመንትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ የሚረዳ ነው ብለዋል።
ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴው የቀረቡ የውሳኔ ሃሳቦችን በመመርመር ሦስቱን ረቂቅ አዋጆች አጽድቋል።
አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...
Sep 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...
Aug 31, 2026
ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Aug 17, 2026
ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...
Jul 27, 2026