የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ያስከበረችውን ስትራቴጂክ ጥቅም በቀይ ባሕር የመድገም ሕጋዊና ተፈጥሯዊ መብት አላት

Jul 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 10 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ያስከበረችውን ስትራቴጂክ ጥቅም በቀይ ባሕር የመድገም ሕጋዊና ተፈጥሯዊ መብት አላት ሲሉ አሜሪካዊው የፖለቲካ ተንታኝ አንድሪው ኮሪብኮ ገለጹ።

ሕዳሴ ግድብ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን የሚያፋጥን ስትራቴጂካዊ የልማት ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።

አንድሪው ኮሪብኮ እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት የተስተካከለ የውሃ ፍሰት በመፍጠር፣የጎርፍ መጥለቅለቅንና የውሃ ብክነትን የታደገ አህጉራዊ ፕሮጀክት ነው።


ኢትዮጵያ ግድቡን መገንባቷ ሀገራዊና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ዕድገትን የሚያፋጥን የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር አቅም እንዲጎለብት ማስቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም ለምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የሚላከው የኤሌክትሪክ ኃይል፣ቀጣናዊ ትብብርን በማጎልበት ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ውህደት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን የገነባችበት መንገድ፣በታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል የሚለውን የግብፅ መሰረተ ቢስ አጀንዳ ሙሉ ለሙሉ የቀለበሰ መሆኑን አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ያስከበረችውን ስትራቴጂክ ጥቅም በቀጣይም በቀይ ባሕር የመድገም ሕጋዊና ተፈጥሯዊ መብት እንዳላት አብራርተዋል።


የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የሚከተሉት ስትራቴጂ በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋሪ ግፊትና በተላላኪዎች አማካይነት የሚፈጸም መሆኑን ጠቁመዋል።

ስግብግብ ፍላጎትና በሌሎች ሀገር ላይ የሚጫን ተስፋፊነትን ያነገቡ የግብፅ ገዥ መደቦች በኢትዮጵያ ውስጥና በኤርትራ የሚገኙ ፅንፈኛና ታጣቂ ቡድኖችን እንደ መሳሪያ በመጠቀም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማደናቀፍ በተደጋጋሚ ሲሞክሩ መስተዋላቸውን አውስተዋል።

ይህ የማያዋጣ አካሄድ መሆኑን በመጠቆም በተፋሰሱ ሀገራት የሚነሱ የውሃ ሀብት አጠቃቀም ጥያቄዎችን፣የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ በሚል መርህ በሰለጠነ ውይይትና በጋራ ተጠቃሚነት መፍታት እንደሚቻል አስረድተዋል።

የዓባይ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ውጥረት ከሚያባብስ አካሄድ ሊቆጠቡ ይገባል ያሉት ተንታኙ፥ ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋትን በማስቀደም የጋራ ብልፅግናን የሚያረጋግጥ ትብብር ማድረግ እንደሚኖርባቸው አፅንኦት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8/2018 ( አዜአ) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ኤሎምቢ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።...

Jul 17, 2026

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...

Jul 9, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...

Jul 9, 2026

የሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በ...

Jul 7, 2026