የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነት ማሳደጉን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው፣ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም፤ መንግሥት የጀመራቸው አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ተከታታይ ዕድገት እንዲያስመዘግብ ማስቻሉን ገልጸዋል።

ግብርና 7 ነጥብ 7 በመቶ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዘንድሮ 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ኩንታል ምርት ተሰብስቧል ብለዋል።

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማስፋፋትና ለማዘመን ከተያዙ ቁልፍ ዘርፎች መካከል የኢንዱስትሪው ክፍለ-ኢኮኖሚ ዋነኛውና የትኩረት ማዕከል መሆኑን ጠቅሰዋል።

ከለውጡ በፊት በሀገሪቱ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ በታች የነበረው የማምረት አቅም አሁን ላይ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል።


በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ እንዳሉት፤ በአምስት ዓመታት የምክር ቤት ዘመን ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እመርታን አስመዝግባለች።

በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመትም በብዝኅ ኢኮኖሚ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት የተኪ ምርት አቅምን በማሳደግ በወጪ ንግድ ጭምር ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአመራር ቁርጠኝነት፣ የዜጎች ትብብርና የመሪነት ሚናም ኢትዮጵያ ላስመዘገበችው እመርታ ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከቱን አንስተዋል።



በምክር ቤቱ የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አራሬ ሞሲሳ በበኩላቸው፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በርካታ አዋጆች በማፅደቅ ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር የህዝብ ውክልና ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ባለፉት ዓመታት በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ፕሮጀክቶች እንዲገነቡ በማስቻልና የከተማ ገፅታን በመቀየር በርካታ ስኬቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል።



የምክር ቤቱ አባል መስፍን እርካቤ፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ጥያቄና ችግሮች ምላሽ እያገኙ ምርታማነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።



ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት የገጠሟትን የውስጥና የውጭ ፈተናዎች ተቋቁማ በሁሉም ዘርፎች የተሻለ ውጤት አስመዝግባለች ያሉት ደግሞ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት አቡኔ አለም ናቸው።

የምክር ቤት አባላቶቹ እየተከናወኑ የሚገኙት ውጤታማ የልማት ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026