🔇Unmute
ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ።
በዘጠና ቀናት ዕቅድና አፈጻጸም ላይ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በደሴ ከተማ ውይይት እያካሄዱ ነው።

የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የክልሉን ዕድገትና የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ አመራር በመስጠት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
በክልሉ በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በዚህም የክረምት ሥራዎችን ጨምሮ በዋና ዋና የልማት ዘርፎች ላይ በመረባረብ፣ የተጀመረውን ዕድገትና ብልፅግና ዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አክለዋል።

በተለይም በየደረጃው ያለው አመራር የመረጠውን ሕዝብ በላቀ ሁኔታ ለማገልገልና ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል።
ለዚህም የመንግሥትን አፈጻጸም በሁሉም ዘርፍ ማሳደግ፣የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት፣ የዜጎችን ገቢ ማላቅና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ማስፋፋት ላይ በማተኮር ችግሮችን የመፍታት አቅጣጫ መከተል እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል።
የክልሉን ሰላም ለማጽናት በተደረገው ጥረት ውጤታማ ተግባር መከናወኑን የጠቆሙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በቀጣይም ሰላሙን በዘላቂነት በመጠበቅ ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በመድረኩም ላይ የክልል፣የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...
Jul 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...
Jul 9, 2026
ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በ...
Jul 7, 2026
ወላይታ ሶዶ ፤ ሰኔ 24/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትን በመጠቀም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የ...
Jul 3, 2026