የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

Jul 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለጹ።

በዘጠና ቀናት ዕቅድና አፈጻጸም ላይ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በደሴ ከተማ ውይይት እያካሄዱ ነው።


የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የክልሉን ዕድገትና የሕብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጠናከረ አመራር በመስጠት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።

በክልሉ በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በዚህም የክረምት ሥራዎችን ጨምሮ በዋና ዋና የልማት ዘርፎች ላይ በመረባረብ፣ የተጀመረውን ዕድገትና ብልፅግና ዳር ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አክለዋል።


በተለይም በየደረጃው ያለው አመራር የመረጠውን ሕዝብ በላቀ ሁኔታ ለማገልገልና ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል።

ለዚህም የመንግሥትን አፈጻጸም በሁሉም ዘርፍ ማሳደግ፣የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት፣ የዜጎችን ገቢ ማላቅና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ማስፋፋት ላይ በማተኮር ችግሮችን የመፍታት አቅጣጫ መከተል እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል።

የክልሉን ሰላም ለማጽናት በተደረገው ጥረት ውጤታማ ተግባር መከናወኑን የጠቆሙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በቀጣይም ሰላሙን በዘላቂነት በመጠበቅ ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በመድረኩም ላይ የክልል፣የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026