የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ገለጹ።

የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለማስጀመር የሚያስችልና አባል ሀገራትን መግባባት ላይ የሚያደርስ ልዩ ስብሰባ ማካሄድ ጀምሯል።

ይህ መድረክ አባል ሀገራትን መግባባት ላይ ለማድረስና የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለመክፈት ያለመ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣናው አስተማማኝና ዘላቂ አቅርቦት ለመፍጠር የምታደርገውን ጥረት እንደሚያሳይ ገልጸዋል።

ይህ የኃይል ትስስር ለኢትዮጵያ ትልቅ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ባለፈ፣ በአባል ሀገራቱ መካከል በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ዘርፎች ጠንካራ መስተጋብር እንዲፈጠር እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

በአሁን ወቅት ይህንን ቀጣናዊ መስተጋብር ወደ አንድ የጋራ የአፍሪካ የኃይል ትስስር ለማሳደግ መጠነ-ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል።


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) ሊቀመንበር ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፤ የኃይል ትስስሩ ለሀገር በርካታ ጥቅሞች እንዳሉት አብራርተዋል።

የኢትዮጵያን ቀጣናዊ ተሰሚነትና የዲፕሎማሲ አቅም ከማሳደግ ባለፈ፤ ከኃይል ሽያጭ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ እያስቻላት መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት ከኬንያ፣ ሱዳን፣ ጂቡቲና ታንዛኒያ ጋር ስምምነት በመፍጠር ኃይል እያቀረበች መሆኗን ጠቁመዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም፤ በቀጣይም ከደቡብ ሱዳን እና ከሶማሊያ ጋር የኃይል ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን ...

Jul 9, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ምርታማነትን በማሻሻል የዘርፎችን ውጤታማነት አሳድጓል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የተከተለችው የብዝኅ-ዘርፍ ኢኮኖሚ ትግበራ ስኬታማ የሪፎርም ሥራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የዘርፎችን ውጤታማነ...

Jul 9, 2026

የሕዝብን የልማት ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቷል-አብዱ ሁሴን (ዶ/ር)

ደሴ፤ሰኔ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት የሕዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በጥናት ላይ ተመስርቶ በፍጥነት ለመመለስ በ...

Jul 7, 2026

በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

ወላይታ ሶዶ ፤ ሰኔ 24/2018(ኢዜአ)፦ በወላይታ ዞን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ሂደትን በመጠቀም ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የ...

Jul 3, 2026