የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የቀጣናውን የኃይል ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ገለጹ።

የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለማስጀመር የሚያስችልና አባል ሀገራትን መግባባት ላይ የሚያደርስ ልዩ ስብሰባ ማካሄድ ጀምሯል።

ይህ መድረክ አባል ሀገራትን መግባባት ላይ ለማድረስና የቀጣናውን የኃይል ንግድ በይፋ ለመክፈት ያለመ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።


የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣናው አስተማማኝና ዘላቂ አቅርቦት ለመፍጠር የምታደርገውን ጥረት እንደሚያሳይ ገልጸዋል።

ይህ የኃይል ትስስር ለኢትዮጵያ ትልቅ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ባለፈ፣ በአባል ሀገራቱ መካከል በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ዘርፎች ጠንካራ መስተጋብር እንዲፈጠር እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

በአሁን ወቅት ይህንን ቀጣናዊ መስተጋብር ወደ አንድ የጋራ የአፍሪካ የኃይል ትስስር ለማሳደግ መጠነ-ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል።


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) ሊቀመንበር ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፤ የኃይል ትስስሩ ለሀገር በርካታ ጥቅሞች እንዳሉት አብራርተዋል።

የኢትዮጵያን ቀጣናዊ ተሰሚነትና የዲፕሎማሲ አቅም ከማሳደግ ባለፈ፤ ከኃይል ሽያጭ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ እያስቻላት መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት ከኬንያ፣ ሱዳን፣ ጂቡቲና ታንዛኒያ ጋር ስምምነት በመፍጠር ኃይል እያቀረበች መሆኗን ጠቁመዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም፤ በቀጣይም ከደቡብ ሱዳን እና ከሶማሊያ ጋር የኃይል ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረግ ጥረት ይቀጥላል

አሶሳ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት ሁለንተናዊ እድገትና የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን የማድረ...

Sep 11, 2026

በመደመር መንግሥት ዕይታ አዲስ አበባን የብልጽግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ) ፦በቀጣይ አምስት ዓመታት በዘላቂ የልማት ሥራዎች ላይ አፈፃፀማችንን በማላቅ ሕዝባችን የሰጠንን ሀላፊነት በብቃት መወ...

Aug 31, 2026

በአፋር ክልል የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ይጠናከራሉ

ሰመራ፣ነሀሴ 10/2018 (ኢዜአ):- በአፋር ክልል በተያዘው በጀት ዓመት የገቢ አማራጮችን የማስፋትና በቁርጠኝነት ገቢን የመሰብሰብ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Aug 17, 2026

በሸገር ከተማ አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ተደርጓል

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት አርሶ አደሩን በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታ...

Jul 27, 2026