የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአሜሪካዊው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የሙስና ወንጀል ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል

Jan 13, 2025

IDOPRESS

ሴናተሩ ሰርተውታል በተባሉበትና በተከሰሱበት ወንጀል በደረሰባቸው ጫና ምክንያት ከሃላፊነታቸው ለመልቀቅ ማመልከቻቸውን ለኒው ጄርሲው አገረ ገዥ ፊል መርፊ ማስገባታቸውን የዛሬው የሲቢኤስ ኒውስ ዘገባ ያሳያል።

ይሄንን ተከትሎም በአሜሪካ በመጪው ህዳር ላይ በሚደረገው ምርጫ እንደማይሳተፉም በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እየወጡ ያሉ መረጃዎች ያመለክታሉ።

ሴናተር ቦብ ሚኔንዴዝ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ በኒውጄርሲ በንግድ ስራ ላይ ከተሰማሩ 3 የግብጽ ሰዎች እጅ ወርቅ እና ጥሬ ገንዘብ ጉቦ መቀባላቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

ይህም ሴናተሩ ራሳቸውን ለግብጽ መንግሥት ወኪል አድርገው በመቆም ሰርተዋል የሚል ክስ ሲቀርብባቸው እንደነበረ ይታወቃል።

በዚህም በዘረፋ፣ ጉቦ በመቀበል፣ ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም፣ በሴራ፣ ፍትህን በማደናቀፍና መሰል 16 ወንጀሎች ላይ ተሳትፎ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑም ተመላክቷል፡፡

በመሆኑም በሚቀጥለው ህዳር ወር በሚካሄደው ምርጫ ዴሞክራቶችን ወክለው የሚወዳደሩት ቦብ ሜኒዴዝ ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንዲለቁ መሆናቸውን ተከትሎም በሌላ እጩ እንደሚተኩ ተገልጿል።

የ70 ዓመት አዛውንቱ ሴናተር ቦብ ሚኒንዴዝ ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮችን ከሀገሪቱ ወታደራዊ እርዳታ ማመቻቸታቸውም ከተከሰሱባቸው ጉዳዮች አንዱ ሆኖ ቀርቧል።

አጋሮቻቸውን ከወንጀል በመከላከል፣ አለአግባብ እንዲበለጽጉ በባለቤታቸው በኩል ከግብጽ የደህንነት ሰዎች ጋር ግኑኝነት በመፍጠር ስልጣንን አላግባብ ተጠቅመዋል ሲል አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል።

የውጭ ጉዳይ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሊቀ-መንበር ሆነው ስራቸውን እየሰሩ ስለመሆናቸው የሚናገሩት ቦብ ሚኔንዴዝ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሳምንታት ያክል ምርመራ ሲደረግባቸው እንደቆየ ቢገለጽም እሳቸው አሁንም አልፈጸምኩም እያሉ ይገኛሉ።

ሴናተሩ “እኔ በህዝብ ፊት የገባሁትን ቃል አልጣስኩም፣ ከሀገር ወዳድነቴና አርበኝነቴ ውጭ ምንም አልሆንኩም ለማንም ሀገር የምሰራው ጉዳይ የለኝም” ማለታቸውም ተገልጿል።

እኚህ አዛውንት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በተጠረጠሩበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙና ከተፈረደባቸው ቀሪ ዘመናቸውን በማረሚያ ቤት ሊያሳልፉ እንደሚችሉም አሶሲዬትድ ፕሬስን ጨምሮ የተለያዩ የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡት ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026