
ሴናተሩ ሰርተውታል በተባሉበትና በተከሰሱበት ወንጀል በደረሰባቸው ጫና ምክንያት ከሃላፊነታቸው ለመልቀቅ ማመልከቻቸውን ለኒው ጄርሲው አገረ ገዥ ፊል መርፊ ማስገባታቸውን የዛሬው የሲቢኤስ ኒውስ ዘገባ ያሳያል።
ይሄንን ተከትሎም በአሜሪካ በመጪው ህዳር ላይ በሚደረገው ምርጫ እንደማይሳተፉም በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እየወጡ ያሉ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሴናተር ቦብ ሚኔንዴዝ በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ በኒውጄርሲ በንግድ ስራ ላይ ከተሰማሩ 3 የግብጽ ሰዎች እጅ ወርቅ እና ጥሬ ገንዘብ ጉቦ መቀባላቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
ይህም ሴናተሩ ራሳቸውን ለግብጽ መንግሥት ወኪል አድርገው በመቆም ሰርተዋል የሚል ክስ ሲቀርብባቸው እንደነበረ ይታወቃል።
በዚህም በዘረፋ፣ ጉቦ በመቀበል፣ ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም፣ በሴራ፣ ፍትህን በማደናቀፍና መሰል 16 ወንጀሎች ላይ ተሳትፎ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑም ተመላክቷል፡፡
በመሆኑም በሚቀጥለው ህዳር ወር በሚካሄደው ምርጫ ዴሞክራቶችን ወክለው የሚወዳደሩት ቦብ ሜኒዴዝ ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንዲለቁ መሆናቸውን ተከትሎም በሌላ እጩ እንደሚተኩ ተገልጿል።
የ70 ዓመት አዛውንቱ ሴናተር ቦብ ሚኒንዴዝ ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮችን ከሀገሪቱ ወታደራዊ እርዳታ ማመቻቸታቸውም ከተከሰሱባቸው ጉዳዮች አንዱ ሆኖ ቀርቧል።
አጋሮቻቸውን ከወንጀል በመከላከል፣ አለአግባብ እንዲበለጽጉ በባለቤታቸው በኩል ከግብጽ የደህንነት ሰዎች ጋር ግኑኝነት በመፍጠር ስልጣንን አላግባብ ተጠቅመዋል ሲል አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል።
የውጭ ጉዳይ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሊቀ-መንበር ሆነው ስራቸውን እየሰሩ ስለመሆናቸው የሚናገሩት ቦብ ሚኔንዴዝ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለሳምንታት ያክል ምርመራ ሲደረግባቸው እንደቆየ ቢገለጽም እሳቸው አሁንም አልፈጸምኩም እያሉ ይገኛሉ።
ሴናተሩ “እኔ በህዝብ ፊት የገባሁትን ቃል አልጣስኩም፣ ከሀገር ወዳድነቴና አርበኝነቴ ውጭ ምንም አልሆንኩም ለማንም ሀገር የምሰራው ጉዳይ የለኝም” ማለታቸውም ተገልጿል።
እኚህ አዛውንት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በተጠረጠሩበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙና ከተፈረደባቸው ቀሪ ዘመናቸውን በማረሚያ ቤት ሊያሳልፉ እንደሚችሉም አሶሲዬትድ ፕሬስን ጨምሮ የተለያዩ የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡት ይገኛሉ።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026