የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ለግብርና ቆጠራ መረጃ አሰባሰብ ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር ጠየቀ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

ባሌ ሮቤ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ እያካሄደ ለሚገኘው የግብርና ቆጠራ መረጃ አሰባሰብ ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር ጠየቀ።

አገልግሎቱ ከባ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖች ለተውጣጡ ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ሥልጠና በሮቤ ከተማ እየሰጠ ነው።


በአገልግሎቱ የቢዝነስ ታትስቲክስ መሪ ሥራ አስፈፃሚ እና የሁለቱ የባሌ ዞኖችና የምዕራብ አርሲ ዞን የግብርና ቆጠራ የክላስተር አስተባባሪ አቶ ናቃቸው ነጋሽ እንዳሉት፣ የስታትስቲክስ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ የግብርና ናሙና ቆጠራ ማካሄድ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።

አገልግሎቱ በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሙያዎችን መልምሎ ካሰለጠነ በኋላ ወደ መስክ በማሰማራት ተጨባጭ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

በሁለቱ የባሌ ዞኖችና ከፊል የምዕራብ አርሲ ዞን የተውጣጡ 833 የሚሆኑ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ወስደው የመስክ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።

የቤተሰብ ምዝገባና መረጣ፣ የሰብል ምርትና ምርታማነት ግምገማ፣ የእንስሳት ቆጠራ ሥራዎች እስከ አሁን ከተከናወኑ ሥራዎች መካከል ናቸው።

ከሁለቱ የባሌ ዞኖች ለተውጣጡ ባለድርሻ አካላት የተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ባለድርሻ አካላት ስለ ግብርና ቆጠራው ጥልቅ ግንዛቤ ኖሯቸው ለመረጃ አሰባሰቡ ውጤታማነት እገዛ እንዲያደርጉ ለማነሳሳት ነው።

ባለድርሻ አካላት ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።


በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የባሌ ጎባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሽመልስ አሰፋ በበኩላቸው፣ የባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ሥልጠና በግብርና ቆጠራው ፕሮግራም የጠራ መረጃ በማሰባሰብ ለሚፈለገው ሀገራዊ ዓላማ እንዲውል እገዛ እንዲያደርጉ ያግዛል ብለዋል።

በስካሁኑ ሂደት ከግንዛቤ እጥረትና ሌሎች በዘርፉ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ እገዛው ከፍተኛ መሆኑንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ሁለተኛው ዙር የግብርና ናሙና ቆጠራ ለበርካታ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መግባቱን የአገልግሎቱ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026