
ባሌ ሮቤ፤ ጥር 3/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ እያካሄደ ለሚገኘው የግብርና ቆጠራ መረጃ አሰባሰብ ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር ጠየቀ።
አገልግሎቱ ከባ እና ምስራቅ ባሌ ዞኖች ለተውጣጡ ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ሥልጠና በሮቤ ከተማ እየሰጠ ነው።

በአገልግሎቱ የቢዝነስ ታትስቲክስ መሪ ሥራ አስፈፃሚ እና የሁለቱ የባሌ ዞኖችና የምዕራብ አርሲ ዞን የግብርና ቆጠራ የክላስተር አስተባባሪ አቶ ናቃቸው ነጋሽ እንዳሉት፣ የስታትስቲክስ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ የግብርና ናሙና ቆጠራ ማካሄድ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
አገልግሎቱ በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሙያዎችን መልምሎ ካሰለጠነ በኋላ ወደ መስክ በማሰማራት ተጨባጭ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
በሁለቱ የባሌ ዞኖችና ከፊል የምዕራብ አርሲ ዞን የተውጣጡ 833 የሚሆኑ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ወስደው የመስክ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።
የቤተሰብ ምዝገባና መረጣ፣ የሰብል ምርትና ምርታማነት ግምገማ፣ የእንስሳት ቆጠራ ሥራዎች እስከ አሁን ከተከናወኑ ሥራዎች መካከል ናቸው።
ከሁለቱ የባሌ ዞኖች ለተውጣጡ ባለድርሻ አካላት የተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ባለድርሻ አካላት ስለ ግብርና ቆጠራው ጥልቅ ግንዛቤ ኖሯቸው ለመረጃ አሰባሰቡ ውጤታማነት እገዛ እንዲያደርጉ ለማነሳሳት ነው።
ባለድርሻ አካላት ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።

በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የባሌ ጎባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሽመልስ አሰፋ በበኩላቸው፣ የባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ሥልጠና በግብርና ቆጠራው ፕሮግራም የጠራ መረጃ በማሰባሰብ ለሚፈለገው ሀገራዊ ዓላማ እንዲውል እገዛ እንዲያደርጉ ያግዛል ብለዋል።
በስካሁኑ ሂደት ከግንዛቤ እጥረትና ሌሎች በዘርፉ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲፈቱ እገዛው ከፍተኛ መሆኑንም አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ሁለተኛው ዙር የግብርና ናሙና ቆጠራ ለበርካታ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መግባቱን የአገልግሎቱ መረጃ ያመለክታል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026