
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል የኮሪደር ልማት ስራዎች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተመልክተዋል።
አቶ ኦርዲን በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኮሪደር ልማት ስራው በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።

በተለይም በከተማው በ1 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው የአባድር ፕላዛ በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ከግንባታው ስራ ጎን ለጎን እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተናግረዋል።
የአባድር ፕላዛ አካባቢውን ባማከለ መልኩ ከዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ ጋር በማስተሳሰር እየተከናወነ እንደሚገኝና የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር በማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው አመራሩ የራሱን ሚና ሊጫወት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ ማሳሰባቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026