
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ204 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለወጪ ገበያ በመላክ ከ908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ዑመር ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ከቡና ውጪ ንግድ 2 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።
በዚህም ወደ ውጭ ከተላከው ከ204 ሺህ 206 ቶን ቡና ውስጥ ባለፉት ስድስት ወራት 908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኙቱን ተናግረዋል።
ይህም በዕቅዱ አንጻር 127 በመቶ ብልጫ ያለው ገቢ መሆኑን ጠቁመው፤ አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ከተገኘው 571 ሚሊየን ጋር ሲነጻጻር ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣይ ወራትም የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026