
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ204 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለወጪ ገበያ በመላክ ከ908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ዑመር ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ከቡና ውጪ ንግድ 2 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።
በዚህም ወደ ውጭ ከተላከው ከ204 ሺህ 206 ቶን ቡና ውስጥ ባለፉት ስድስት ወራት 908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኙቱን ተናግረዋል።
ይህም በዕቅዱ አንጻር 127 በመቶ ብልጫ ያለው ገቢ መሆኑን ጠቁመው፤ አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ከተገኘው 571 ሚሊየን ጋር ሲነጻጻር ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣይ ወራትም የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026