የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም ከነገ ጀምሮ በፓሪስ ይካሄዳል

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 23/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ተቋማት የሚሳተፉበት የኢትዮጵያ-አውሮፓ ህብረት ኢንቨስትመንት ፎረም ከነገ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም ጀምሮ በፈረንሳይ ፓሪስ ይካሄዳል፡፡

ፎረሙ የሁለቱን አካላት ግንኙነት ለማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል፡፡

በዚህም የፈረንሳይ ድርጅቶች በአለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲኖራቸው የሚሰራ እና የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በሚደግፈው ሜዴፍ ኢንተርናሽናል እና በአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በአራት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ማለትም በአቪየሽን፤ በታዳሽ ሃይል፤ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሰረተልማት እና በዲጂታል ቴሌኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም የኢትዮጵያን ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እና እያደረገች ያለውን ሪፎርም በማሳየት የንግድ ትብብርን ለማጠናከር እና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እድል እንደሚኖረው ተመላክቷል፡፡

እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት ለሀገሪቱ ቀጣይነት ያለውን እና አካታች ልማትን ለመደገፍ የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያጠናክር ያግዛል ተብሏል።

ፎረሙን በተመለከተ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ፎረሙ አውሮፓ እና ኢትዮጵያን በፈጠራና በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር አካታች የሆነ እድገት ለማምጣት ትልቅ እርምጃ ነው።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በበኩላቸው፣ኢትዮጵያ በአዲስ የእድገትና የልማት ዘመን ላይ መሆኗን በመግለፅ፥ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የ10 አመቱ የልማት እቅድን በመተግበር የማይናወጥና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ እየገነባች መሆኑን ተናግረዋል።

የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት የግል ዘርፉ ደግሞ ይህንን የልማት እቅድ ለማሳካት ዋና የልማት አጋር መሆኑን አብራርተዋል።

የሜዴፍ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፊሊፕ ጉቶር በበኩላቸው፥ የአውሮፓ የንግድና ኢንቨስትመንት ተቋማት ኢትዮጵያ ትልቅ አቅም እንዳላት ይገነዘባሉ ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ በፍጥነት በማደግ ላይ ያለ ኢኮኖሚ ያላት ሀገር ብቻ ሳትሆን በአረንጓዴ ልማት ፣ዲጂታል እና ትራንስፖርት መሰረተ ልማት ለመገንባት ባላት አቅም ተመራጭ መሆኗን ጠቁመዋል።

የአውሮፓ ህብረት እና ኢትዮጵያ የንግድ፣ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማጎልበት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ፎረምም ይህንን እያደገ ያለ ትብብር ያሳያል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026