🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 26/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር፣ ለጋራ ተጠቃሚነትና ለቀጣናው ደኅንነት መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ምሁራን ገለጹ።
ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን እንደገለጹት፤ የሀገሪቱ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የህልውና እና የቀጣናዊ እድገት ጉዳይ ነው።
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ ዱጋሳ ሙሉጌታ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገዶችን ተከትላ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የሚበረታታ ነው።

የባህር በር ማግኘት የህልውና ጉዳይ መሆኑን አስረድተው፤ ለወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ እንዲሁም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ፍትሐዊ፣ ሕጋዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ-ምድራዊ እውነታን መሰረት ያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀጣናዊ ትስስርን በማጎልበት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሠረተ መሆኑንና ለቀጣናው ሀገራት ዘላቂ ሰላምና የጋራ ልማት የላቀ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል።
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት መምህርና ተመራማሪ ሲሳይ ደመቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የባህር በር ከሸቀጥ ዝውውር ባለፈ የሃሳብ፣ የቴክኖሎጂና የቱሪዝም ፍሰትን በማሳለጥ በኩል ያለውን ፋይዳ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር፣ ለጠንካራ ደህንነት፣ ለኢኮኖሚና ለቴክኖሎጂ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የሎጂስቲክስ ወጪን በመቀነስ የገቢና ወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን፣ ለቀጣናው ደህንነት መጠበቅ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026