የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን ለማስጠበቅ እና ለጋራ ዕድገት ወሳኝ ነው

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 26/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር፣ ለጋራ ተጠቃሚነትና ለቀጣናው ደኅንነት መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ምሁራን ገለጹ።

ኢዜአ ያነጋገራቸው ምሁራን እንደገለጹት፤ የሀገሪቱ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የህልውና እና የቀጣናዊ እድገት ጉዳይ ነው።

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህርና ተመራማሪ ዱጋሳ ሙሉጌታ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገዶችን ተከትላ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የሚበረታታ ነው።


የባህር በር ማግኘት የህልውና ጉዳይ መሆኑን አስረድተው፤ ለወጪና ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ እንዲሁም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ፍትሐዊ፣ ሕጋዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ-ምድራዊ እውነታን መሰረት ያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቀጣናዊ ትስስርን በማጎልበት፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ የተመሠረተ መሆኑንና ለቀጣናው ሀገራት ዘላቂ ሰላምና የጋራ ልማት የላቀ ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል።

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት መምህርና ተመራማሪ ሲሳይ ደመቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የባህር በር ከሸቀጥ ዝውውር ባለፈ የሃሳብ፣ የቴክኖሎጂና የቱሪዝም ፍሰትን በማሳለጥ በኩል ያለውን ፋይዳ አብራርተዋል።


የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ለምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ትስስር፣ ለጠንካራ ደህንነት፣ ለኢኮኖሚና ለቴክኖሎጂ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የሎጂስቲክስ ወጪን በመቀነስ የገቢና ወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን፣ ለቀጣናው ደህንነት መጠበቅ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026