የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በለውጡ ዓመታት የኃይል ማመንጫ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋትና በማዘመን የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ማሻሻል ተችሏል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2018(ኢዜአ)፦ በለውጡ ዓመታት የኃይል ማመንጫ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋትና በማዘመን የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ማሻሻል መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ገለጹ፡፡


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎች በዋናነት በታዳሽ ኃይል (በውኃ፣ በንፋስና በፀሐይ) ላይ ያተኮሩ መሆናቸው፣ ሀገሪቱ ከዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ጋር የተጣጣመ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ለያዘችው ስትራቴጂ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።


በዚህም የአህጉሪቱ የታዳሽ ኃይል ልማት ማዕከልነቷን ለማረጋገጥ በጀመረችው ጉዞ ያስመዘገበቻቸውን ተጨባጭ ውጤቶች አጠናክራ ቀጥላለች፡፡


ኢትዮጵያ በታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም፣ የአፍሪካ ሕብረትን የ2063 አጀንዳ ለማሳካትና አህጉሪቱን በኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተሳሰር ቁልፍ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።


ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የአይሻ 2 እና የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች በስኬት ተጠናቅቀው ወደ ሥራ በመግባታቸው የሀገሪቱ የኃይል ማምረት አቅም ከ9 ሺህ 752 ሜጋ ዋት በላይ ደርሷል።


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል፡፡


በኢትዮጵያ ከከተሞች ዕድገት፣ ከኢንዱስትሪዎች መስፋፋት፣ ከዲጂታል ሽግግር ጋር በተያያዘ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት እንዲጨምር ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል፡፡


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዘመኑ የሚጠይቀውን ኃይል በማቅረብ የዜጎችን ፍላጎት ለማርካት የተጠናከረ የማስፋፊያና የማዘመን ሥራዎችን አከናውኗል ብለዋል፡፡


መንግሥት በለውጡ ዓመታት የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ማስፋፋትና ማዘመን፣ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መገንባት መቻሉን ገልጸዋል፡፡


በኢትዮጵያ 44 በመቶ የነበረው የኃይል ተደራሽነት ሽፋን ባለፉት ሰባት ዓመታት የኃይል መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት ሽፋኑን ወደ 54 በመቶ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል፡፡


ከሰባት ዓመት በፊት ኃይል የማመንጨት አቅም 4ሺህ 462 ሜጋ ዋት እንደነበረ በማስታወስ፤ አሁን ወደ 9 ሺህ 752 ከፍ ማድረግ እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡


የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከሚያመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝ ገልጸው፤ ግድቡ ለሀገራዊ የኃይል ማመንጨት አቅም ዕድገት ገንቢ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡


ሀገራዊ የኃይል አቅርቦት ፍላጎትን ለመመለስ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን በማንሳት፤ የኢትዮጵያ ፈጣን ዕድገት የሚመጥን የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ቀሪ ሥራዎች እንዳሉ ገልጸዋል፡፡


የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታና ማስፋፊያ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸመውን ስርቆት መከላከል ከሁሉም አካላት ይጠበቃል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026