የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ መንግስት የገባውን ቃል በመተግበር የህዝቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ ነው  

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦የክልሉ መንግስት የገባውን ቃል በመተግበር የህዝቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለጹ።

በክልሉ የአሪ ዞን ሰሜን አሪ ወረዳ ከ 57 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተገነቡ የንፁህ መጠጥ ውሃና የሳላ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል።


በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲን ጨምሮ የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

በወቅቱም ዋና አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ እንደገለፁት መንግስት የገባውን ቃል በመተግበር የህዝቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ ነው።


ዛሬ ለአገልግሎት የበቁት የሳላ ወንዝ ድልድይ እና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በህዝቡ ዘንድ ለረጅም ዓመታት ጥያቄ ሲነሳባቸው የነበሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

መንግስት የህዝቡን ጥያቄ በመገንዘብ አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት ርብርብ ሲያደርግ እንደነበር ገልፀው፥ ለዚህም ዛሬ የተመረቁ ፕሮጀክቶች ማሳያ እንደሆኑም አመልክተዋል።

የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ በበኩላቸው አካባቢው ስንዴ፣ የቅባት እህሎች፣ ቅመማ ቅመምና ፍራፍሬዎች በስፋት የሚመረቱበት በመሆኑ የመንገድ ግንባታው ለማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።


በተጨማሪም በአካባቢው ቀደም ሲል ከህብረተሰቡ ጥያቄዎች ሲነሳባቸው የነበሩ የጎዛ ጊቻ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት፣ የጎዞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ጎዛ ጤና ጣቢያ ግንባታዎች ተመርቀው ወደ አገልግሎት ገብተዋል ብለዋል።

በቀጣይም የመብራት እና ሌሎች የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚያገኙ አረጋግጠዋል።

በሰሜን አሪ ወረዳ የጎዛ ከተማ ነዋሪዎችም፤ በከተማው መብራት፣ ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ የመንገድ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና ጤና ጣቢያ እንዲገነቡ ሲጠይቁ መቆየታቸውን ገልጸዋል።


ከጥያቄዎቹ መካከል ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ የሳላ ወንዝ ድልድይ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጤና ጣቢያ ግንባታዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት በመብቃታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026