የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ መንግስት የገባውን ቃል በመተግበር የህዝቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ ነው  

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦የክልሉ መንግስት የገባውን ቃል በመተግበር የህዝቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለጹ።

በክልሉ የአሪ ዞን ሰሜን አሪ ወረዳ ከ 57 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተገነቡ የንፁህ መጠጥ ውሃና የሳላ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል።


በፕሮጀክቶቹ ምረቃ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲን ጨምሮ የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

በወቅቱም ዋና አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ እንደገለፁት መንግስት የገባውን ቃል በመተግበር የህዝቡን የልማት ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየመለሰ ነው።


ዛሬ ለአገልግሎት የበቁት የሳላ ወንዝ ድልድይ እና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በህዝቡ ዘንድ ለረጅም ዓመታት ጥያቄ ሲነሳባቸው የነበሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

መንግስት የህዝቡን ጥያቄ በመገንዘብ አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት ርብርብ ሲያደርግ እንደነበር ገልፀው፥ ለዚህም ዛሬ የተመረቁ ፕሮጀክቶች ማሳያ እንደሆኑም አመልክተዋል።

የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ በበኩላቸው አካባቢው ስንዴ፣ የቅባት እህሎች፣ ቅመማ ቅመምና ፍራፍሬዎች በስፋት የሚመረቱበት በመሆኑ የመንገድ ግንባታው ለማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ትልቅ ሚና አለው ብለዋል።


በተጨማሪም በአካባቢው ቀደም ሲል ከህብረተሰቡ ጥያቄዎች ሲነሳባቸው የነበሩ የጎዛ ጊቻ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት፣ የጎዞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትና ጎዛ ጤና ጣቢያ ግንባታዎች ተመርቀው ወደ አገልግሎት ገብተዋል ብለዋል።

በቀጣይም የመብራት እና ሌሎች የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚያገኙ አረጋግጠዋል።

በሰሜን አሪ ወረዳ የጎዛ ከተማ ነዋሪዎችም፤ በከተማው መብራት፣ ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ የመንገድ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና ጤና ጣቢያ እንዲገነቡ ሲጠይቁ መቆየታቸውን ገልጸዋል።


ከጥያቄዎቹ መካከል ንፁህ የመጠጥ ውሃ፣ የሳላ ወንዝ ድልድይ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጤና ጣቢያ ግንባታዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት በመብቃታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026