የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX) በግብርና ምርቶች የኤክስፖርት ቢዝነስ እንዲሁም በቡና ቅምሻና ደረጃ አወጣጥ ዘርፍ ለሦስት ወራት ያሰለጠናቸውን ባለሙያዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ ዘመናዊና ውጤታማ የወጪ ንግድ ሥርዓት ለመገንባት በዕውቀትና በክህሎት የዳበረ የሰው ኃይል ማፍራት ወሳኝ ነው።

በዚህም የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አካዳሚ ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት ረገድ አበረታች ተግባር እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በወጪ ንግድ አስደናቂ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ በተለይም በያዝነው የ2018 በጀት ዓመት አበረታች ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል።

በዚህም ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረው እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ደግሞ ገቢውን ወደ 10 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡


የዛሬዎቹ ሰልጣኞች ይህንን ሀገራዊ የገቢ ግብ ለማሳካትና የወጪ ንግዱን በዕውቀትና በክህሎት ለመምራት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖራቸውም አመላክተዋል።

ተመራቂዎቹም ያገኙትን ዕውቀት ተጠቅመው የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ምሰሶ ሆነው እንዲሰሩ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መርጊያ ባይሳ በበኩላቸው፤ የወጪ ንግድ በዘመናዊ ግብይት ሥርዓት፣ በዕውቀትና በሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲመራ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡


ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የወጪ ንግድ ያላትን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ጥራት ያለው ምርት ለገበያ ማቅረብ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

ለዚህም ለወጪ ንግድ ስኬት ቁልፍ በሆኑት የደረጃ አወጣጥና የጥራት ቁጥጥር ስልጠናዎች በምርት ገበያ አካዳሚ ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

አካዳሚው ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በቡና ቅምሻ ዘርፍ ብቻ ከ3ሺህ 200 በላይ ሰልጣኞችን አሰልጥኖ ያስመረቀ ሲሆን በዘንድሮው ዓመት በግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ቢዝነስ እና በቡና ደረጃ አወጣጥ 168 ባለሙያዎች ማስመረቁን አስታውቀዋል።

የምርት ገበያው አካዳሚ እያስመዘገበ ያለው ስኬት ከሀገር ውስጥ አልፎ አህጉራዊ እውቅናን እያገኘ መምጣቱን የገለጹት አቶ መርጊያ፣ እስካሁን ከ8 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የአካዳሚውን ተሞክሮና ልምድ መቅሰማቸውን ጠቁመዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡ ተመራቂዎች ስልጠናው በዘርፉ የነበራቸውን የተግባር ክፍተት የሞላ፣ ዓለም አቀፍ የገበያ መርሆዎችን በጥልቀት የተረዱበት መሆኑን ተናግረዋል።

አስተያየት የሰጠችው ናርዶስ ተክሌ እንደገለጸችው፤ ስልጠናው ከዚህ ቀደም በልምድ ላይ ተመስርታ ትሠራው የነበረውን አሠራር በሳይንሳዊ የጥራት ደረጃና በቅምሻ ዕውቀት ለመተካት እንደሚያስችላት ገልጻለች፡፡

ተመራቂ ሁሴን አህመድ በበኩሉ፤ ስልጠናው የወጪ ንግድ ሂደቶችን፣ የህግ ማዕቀፎችንና የገበያ ትስስር ስልቶችን በጥልቀት ለመረዳት እንዳስቻለው ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026