የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በዞኑ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታን ከማስፋፋት ጎን ለጎን አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ትኩረት ተደርጓል

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ በኢሉባቦር ዞን የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታን ከማስፋፋት ጎን ለጎን የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና ማሻሻል ትኩረት መደረጉን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

በኢሉባቦር ዞን በበጀት ዓመቱ የተገነቡ 831 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት የማድረግ መርሃ ግብር በሀሉ ወረዳ ተጀምሯል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ አስተዳደሩ ለሕብረተሰቡ ተጠቃሚነት የሚሰራ መሆኑን በተጨባጭ ስራዎች እያሳየ ነው።

በዞኑ በትልቅ በጀት የሚሰሩ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በብዛትና በጥራት ለአገልግሎት በማብቃት ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ተናግረዋል።

በዚህም ዓመት በዞኑ ሁሉም ወረዳዎች የሕብረተሰቡን ጥያቄዎች የሚመልሱ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ቅሬታዎችን የሚፈቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መደረግ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

ከመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ ጎን ለጎን የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና ማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች የሚጠናከሩ መሆኑን አስረድተዋል።

ለምረቃ የበቁት ፕሮጀክቶችም የአስተዳደር ሕንጻዎች፣ ድልድዮች፣ የጤና ተቋማት፣ መንገዶች፣ የሶላር ኃይል ማመንጫ፣ የመጠጥ ውሃና የመስኖ ግድብ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ፣ በክልሉ በበጀት ዓመቱ የበርካታ ፕሮጀክቶች ግንባታ መካሄዱን አስታውሰዋል።

ፕሮጀክቶቹ የልማትና የአገልግሎት ተደራሽነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀሉ ወረዳ ነዋሪዎች ለአገልግሎት እየበቁ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ያለውን አቅም የሚያሳድጉ፤ የሕብረተሰቡንም ማሕበራዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአስተዳደር ሕንጻው ብዙ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን በአንድ ሕንጻ ውስጥ የሚሰበስብ እንደመሆኑ አገልግሎት ለማግኘት የሚጠይቀውን ድካም የሚቀንስ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026