🔇Unmute
ሻሸመኔ ፤ግንቦት 25/2018 (ኢዜአ)፦በጠቅላላ ምርጫው ያሳዩትን ተሳትፎ በማስቀጠል ልማትን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንደሚወጡ የምዕራብ አርሲ ዞን የሻሸመኔ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።
ነዋሪዎቹ ሂደቱን አስመልክተው ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በህዝብ ድምጽ አሸናፊ ሆኖ ከሚመሰረተው መንግስት ጋር በመሆን ልማትን ለማስቀጠል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
በምርጫው የታየው የሕዝብ ንቁ ተሳትፎን በማጎልበት ልማትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም አክለዋል።
አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል የምዕራብ አርሲ ዞን አባ ገዳዎች ሰብሳቢ አባ ገዳ ነጌሶ ገመቹ፤ በጠቅላላ ምርጫው የታየውን የህዝቡን ጠንካራ ተሳትፎ በማስቀጠል ዴሞክራሲን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ ቀበኔ ደሶ፤ በጠቅላላ ምርጫው ህዝቡ ያሳየው ተሳትፎ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሰለጠነ ፖለቲካ ያለውን ዝግጁነትና መንግስት በህዝብ ይሁንታ ብቻ መመስረት እንዳለበት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳያል ብለዋል።
ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ መሠረት ገብረማርያም በበኩላቸው፤ በድምጽ መስጠት ወቅት ያሳየነውን ንቁ ተሳትፎ ቀጣይ ልማትን በማፋጠን እንደግመዋለን ብለዋል።
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026