የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የሻሸመኔ ከተማ ነዋሪዎች በጠቅላላ ምርጫው ያሳዩትን ተሳትፎ በማስቀጠል ልማትን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ገለጹ

Jun 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሻሸመኔ ፤ግንቦት 25/2018 (ኢዜአ)፦በጠቅላላ ምርጫው ያሳዩትን ተሳትፎ በማስቀጠል ልማትን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንደሚወጡ የምዕራብ አርሲ ዞን የሻሸመኔ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

ነዋሪዎቹ ሂደቱን አስመልክተው ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ‎በህዝብ ድምጽ አሸናፊ ሆኖ ከሚመሰረተው መንግስት ጋር በመሆን ልማትን ለማስቀጠል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

በምርጫው የታየው የሕዝብ ንቁ ተሳትፎን በማጎልበት ልማትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም አክለዋል።

አስተያየታቸውን ከሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች መካከል የምዕራብ አርሲ ዞን አባ ገዳዎች ሰብሳቢ አባ ገዳ ነጌሶ ገመቹ፤ በጠቅላላ ምርጫው የታየውን የህዝቡን ጠንካራ ተሳትፎ በማስቀጠል ዴሞክራሲን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

የከተማው ነዋሪ ወይዘሮ ቀበኔ ደሶ፤ በጠቅላላ ምርጫው ህዝቡ ያሳየው ተሳትፎ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሰለጠነ ፖለቲካ ያለውን ዝግጁነትና መንግስት በህዝብ ይሁንታ ብቻ መመስረት እንዳለበት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳያል ብለዋል።

ሌላዋ የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ መሠረት ገብረማርያም በበኩላቸው፤ በድምጽ መስጠት ወቅት ያሳየነውን ንቁ ተሳትፎ ቀጣይ ልማትን በማፋጠን እንደግመዋለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026